የአዳሪ ትምህርት ቤቶች መስፋፋት ጥራት ያለው ተወዳዳሪ ዜጋ ለማፍራት እንደሚያስችል ተገለጸ
ሀዋሳ፡ ሕዳር 12/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የአዳሪ ትምህርት ቤቶች መስፋፋት በክልሉ ጥራት ያለውና ተወዳዳሪ ዜጋ ለማፍራት ያስችላል ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ አስታወቀ።
በኣሪ ዞን ጂንካ ከተማ የኤሶል ልዩ 2ኛ ደረጃ አዳሪ ት/ቤት የክልሉ ማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር አበባየሁ ታደስ በተገኙበት ተመርቆ ተከፍቷል።
የኣሪ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ዳግም መኮንን እንደገለፁት እንደ ሀገር የገጠመንን የትምህርት ስብራት ለመጠገን በአዲሱ የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት እየተተገበሩ ያሉ ሥራዎች አበረታች መሆኑን ገልፀው፥ ትምህርት ቤቱ ለዚህ እንዲበቃ ላደረጉ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
የኣሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም አታ በበኩላቸው ትምህርት ለሁለንተናዊ ለውጥ ያለው ፋይዳ ከፍተኛ መሆኑን በማመን ከወላይታ ሊቃ ት/ቤትና ከአርባምንጭ ባይራ ት/ቤት ተሞክሮ በመውስድ ለዚህ መብቃቱን አስታውሰዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ እና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር አበባየሁ ታደሰ እንዲህ አይነት አዳሪ ት/ቤቶች ለክልላችን ህዝቦች ትልቅ አቅምና ዕድል መሆኑን ተናግረው በሁሉም አከባቢ እንዲህ አይነት አዳሪ ት/ቤቶች ሊስፋፉ እንደሚገባና ሊጠናከሩ እንደሚገባ ተናግረዋል።
አክለውም በአለም ለመወዳደር ዕውቀትን መሠረት ያደረገ፤ ችግር ሊፈታ የሚችልና ጥራት ያለው ተወዳዳሪ ዜጋ ለመፍጠር የሚያስችልና የነበሩ የትምህርት ስብራቶችን በምጠገን ከደህነት ልንወጣ የሚገባን ቁልፍ መሳሪያ ነው ብለዋል።
ትምህርት ቤቱ ለዚህ ምረቃ እንዲበቃ አስተዋጽኦ ላደረጉ የአከባቢው ማህበረሰብና ሌሎችም አካላት ኃላፊው ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
በመጨረሻም የተለያዩ ወረዳዎችና ተቋማት ለትምህርት ቤቱ የሚያስፈልጉ ቁሳቁሶችን ድጋፍ አድርገዋል።
ዘጋቢ: ከተማ በየነ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
ህዝበ ሙስሊሙ የመውሊድ በዓልን ሲያከብር በብዝሃነት ውስጥ የሚንፀባረቁ የመረዳዳትና የአብሮነት በጎ እሴቶችን ይበልጥ በማጠናከር ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ኃላፊና የየዞን ከፍተኛ አመራሮች በሣውላ ማረሚያ ተቋም አረንጓዴ አሻራቸውን በማኖር ልዩ ልዩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ
በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር ምርመራ እና ልየታ ተካሄደ