እምቅ ሀገራዊ ሀብቶቻችን በተሻጋሪ እሳቢያችን በማልማት እንደ ሀገር የተጀመረውን የዕድገት ጉዞ ማስቀጠል እንደሚገባ ተገለጸ
ሀዋሳ፡ ሕዳር 12/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) እምቅ ሀገራዊ ሀብቶቻችን በተሻጋሪ እሳቢያችን በማልማት እንደ ሀገር የተጀመረውን የዕድገት ጉዞ ማስቀጠል አለብን ሲሉ በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ ኢንጂነር አክሊሉ አዳኝ ተናገሩ፡፡
ኢንጂነር አክልሉ በጌዴኦ ዞን ዲላ ከተማ በከተማና መሠረተ ልማት እንቅስቃሴዎች ዙሪያ እየተካሄደ ባለው ህዝባዊ የውይይት መድረክ እንዳሉት፤ የለውጡ መንግስት መምጣትን ተከትሎ ለሀገሪቱ የምጣኔ ሀብት ዕድገትና ለህዝቡ የጋራ ተጠቃሚነት ፋይዳ ያላቸውን እሳቤዎችን በማምጣት ተግባራዊ እያደረገ ነው፡፡
እነዚህን እሳቤዎች ተከትሎ እንደ ሀገር ያሉንን ሀብቶች በመጠቀም የተጀመረውን እንቅስቃሴ ለማስቀጠል ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ ነው ኢንጂነር አክሊሉ ያሳሰቡት፡፡
የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የዲላ ከተማን ሁለንተናዊ ዕድገት ከሌሎች አቻ ከተሞች ጋር እኩል ለማራመድ የተጀመሩ ሥራዎች ቢኖሩም በሚፈለገው ደረጃ ልማቱን ለማፋጠን የህብረተሰቡ ሁለንተናዊ ድጋፍ እንደሚያስፈልግ አስታውቀዋል፡፡
በውይይቱም የሀይማኖት አባቶችና የባህል ሽማግሌዎችን ጨምሮ ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው ባለድርሻዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ፡፡
ዘጋቢ፡ ሳሙኤል በቀለ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
ህብር ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የምርጫ ማኒፌስቶ፣ የዕጩ ማስተዋወቂያ እንዲሁም የምርጫ ቅስቀሳ ፕሮግራም በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ አካሄደ
ኦርቢስ ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ ጥራት ያለው የአይን ህክምና በሀገሪቱ ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየሰራ መሆኑ ተገለፀ
ብልጽግና ፓርቲ የማህበረሰቡ ችግር የሚቀርፉ ፕሮጀክቶችን ገንብቶ በማጠናቀቅ በውጤታማነት ለአገልግሎት እያበቃ ነው – ዶ/ር መሀመድ ኑርዬ