ተቋማት ትክክለኛ እና ጥራት ያላቸውን መረጃዎችን በማደራጀት የበኩላቸውን እንዲወጡ ጥሪ ቀረበ
ሀዋሳ፡ ሕዳር 12/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ለሀገራዊ ዕድገት የሚኖረው ፋይዳ የጎላ በመሆኑ ተቋማት ትክክለኛ እና ጥራት ያላቸውን መረጃዎችን በማደራጀት የበኩላቸውን እንዲወጡ የጎፋ ዞን ፍትህ መምሪያ ጥሪ አቅርቧል።
የጎፋ ዞን ፍትህ መምሪያ የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ዙር ምክር ቤት ጉባኤና 1ኛ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ዙሪያ የምክክር አድርጓል።
ወቅታዊ ጋብቻ፣ የፍቺ፣ የልደት እና የሞት ኩነቶች ምዝገባ አተገባበር ዙሪያ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር ለመምከር ያለመ መሆኑም ተመላክቷል።
ተቋማት የዜጎችን ልደት፣ ጋብቻ፣ ሞትና ፍቺ ኩነቶች መረጃ በመመዝገብ እና በማደራጀት ለሀገራዊ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ፋይዳ የበኩላቸውን እንዲወጡ የጎፋ ዞን ፍትህ መምሪያ ኃላፊ አቶ ደመላሽ ብላቴ አሳስበዋል።
ባለድርሻ አካላት በተለይም ጤና፣ ትምህርት፣ ፐብሊክ ሰርቪስ፣ ፍርድ ቤቶች እንዲሁም ሴቶች ህጻናት ጉዳይ እና የሃይማኖት ተቋማት ዋነኛ ተዋናይ በመሆናቸው ለትክክለኛ መረጃ ጥንቅር የሚሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡
ከባለድርሻ አካላት አንዱ በሆነው ጤና ተቋም በጤና ጣቢያዎች እና ሆስፒታሎች የተጀመረው የልደት እና ሞት ምዝገባ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የጎፋ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ሊቃውንት አዛዜ ገልጸዋል።
በያዝነው ዓመት ከ12ሺህ በላይ ኩነቶችን ለመመዝገብ መታቀዱንና ባለፉት 3 ወራት 1ሺህ 123 የተከናወነ ሲሆን በየኩነት አመዘጋገብ ዙሪያ የህብረተሰቡን አመለካከት ለማሳደግ ሰፊ ስራ እንደሚሰራ የጎፋ ዞን ፍትህ መምሪያ የወሳኝ ኩነቶች ሥራ ሂደት አሰተባባሪ ወ/ሮ ራድያ ገልጸዋል።
ዘጋቢ – ስንታየሁ ሙላቱ – ከሳውላ ጣቢያችን

More Stories
እየተከናወነ ያለውን የኮሪደር ልማት ሥራ ከዳር ለማድረስ በሚደረገው ርብርብ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሙዱላ ከተማ አስተዳደር ገለፀ
በትምህርት ሴክተር የመረጃ አያያዝ ውጤታማነት ዙሪያ በኩረት እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ
ሁሉንም የመማሪያ መጻሕፍት ባለማግኘታቸው በትምህርታቸው ላይ ጫና እየፈጠረባቸው መሆኑን በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የቆንጋና ቆቄ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ተናገሩ