በልማትና መልካም አስተዳደር ችግሮች ዙሪያ የሚመክር ክልል አቀፍ የከተሞች ህዝባዊ የንቅናቄ መድረክ እየተካሄደ ነው
ሀዋሳ፡ ሕዳር 11/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በልማትና መልካም አስተዳደር ችግሮችና የመፍትሔ አቅጣጫዎች ዙሪያ የሚመክር ክልል አቀፍ የከተሞች ህዝባዊ የንቅናቄ መድረክ በጌዴኦ ዞን ገደብ ከተማ እየተካሄደ ነው።
በመድረኩ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተርና የዕለቱ የክብር እንግዳ ዶ/ር መሪሁን ፍቅሩ የንቅናቄ መድረኩ ዋና ዓላማ በሀገር ልማት ዕድገት ውስጥ የከተማና ከተሜነት ድርሻን ማሳደግ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
የከተሞችን የልማትና መልካም አስተዳደር ችግሮችን በመፍታት የህብረተሰቡን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ከማረጋገጥ አኳያ ውይይቱ ከፍተኛ ጠቀሜታ ያለው መሆኑን የከተማው ከንቲባ አቶ ታሪኩ ሮቤ አስረድተዋል፡፡
በንቅናቄ መድረኩ ከከተማ ቀበሌያት የተወጣጡ የግሉ ዘርፍ ባለሀብቶች፣ የንግዱ ማህበረሰብ፣ የመንግስት ሰራተኞች፣ የሀይማኖች አባቶች፣ የባህል ሽማግለዎች እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እየተሳተፉ ይገኛሉ፡፡
ዘጋቢ፡ ሳሙኤል በቀለ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
More Stories
አካል ጉዳተኞች መብቶቻቸውና ጥቅሞቻቸውን ለማስጠበቅ በቅንጅትና በጥምረት መስራት እንደሚገባ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ገለፀ
አካባቢን በመጠበቅና በማጽዳት ምቹና ጽዱ ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት በማገዝ ሁሉም የድርሻውን ልወጣ እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር እንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ አሳሰቡ
ግለሰባዊ ነጠላ ትርክቶችን በጋራ በመታገል በመደመር እሳቤ ችግሮችን መፍታት እንደሚገባ ተገለጸ