በልማትና መልካም አስተዳደር ችግሮች ዙሪያ የሚመክር ክልል አቀፍ የከተሞች ህዝባዊ የንቅናቄ መድረክ እየተካሄደ ነው
ሀዋሳ፡ ሕዳር 11/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በልማትና መልካም አስተዳደር ችግሮችና የመፍትሔ አቅጣጫዎች ዙሪያ የሚመክር ክልል አቀፍ የከተሞች ህዝባዊ የንቅናቄ መድረክ በጌዴኦ ዞን ገደብ ከተማ እየተካሄደ ነው።
በመድረኩ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተርና የዕለቱ የክብር እንግዳ ዶ/ር መሪሁን ፍቅሩ የንቅናቄ መድረኩ ዋና ዓላማ በሀገር ልማት ዕድገት ውስጥ የከተማና ከተሜነት ድርሻን ማሳደግ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
የከተሞችን የልማትና መልካም አስተዳደር ችግሮችን በመፍታት የህብረተሰቡን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ከማረጋገጥ አኳያ ውይይቱ ከፍተኛ ጠቀሜታ ያለው መሆኑን የከተማው ከንቲባ አቶ ታሪኩ ሮቤ አስረድተዋል፡፡
በንቅናቄ መድረኩ ከከተማ ቀበሌያት የተወጣጡ የግሉ ዘርፍ ባለሀብቶች፣ የንግዱ ማህበረሰብ፣ የመንግስት ሰራተኞች፣ የሀይማኖች አባቶች፣ የባህል ሽማግለዎች እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እየተሳተፉ ይገኛሉ፡፡
ዘጋቢ፡ ሳሙኤል በቀለ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
More Stories
ጥራት ያለው የጤና አገልግሎትን ለማህበረሰቡ ተደራሽ ለማድረግ የጤና ባለሙያዎች በኃላፊነት ሊሰሩ እንደሚገባ በጌዴኦ ዞን የይርጋጨፌ ወረዳ አስተዳደር አስታወቀ
የባስኬቶ ዞን ተወላጆች የአንድነት መድረክ ማጠቃለያ እየተካሄደ ነው
በእንስሳት እርባታ ከተሰማራን ወዲህ ኑሯችን ተሻሽሏል – የጋዘር ከተማ ወጣቶች