በልማትና መልካም አስተዳደር ችግሮች ዙሪያ የሚመክር ክልል አቀፍ የከተሞች ህዝባዊ የንቅናቄ መድረክ እየተካሄደ ነው
ሀዋሳ፡ ሕዳር 11/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በልማትና መልካም አስተዳደር ችግሮችና የመፍትሔ አቅጣጫዎች ዙሪያ የሚመክር ክልል አቀፍ የከተሞች ህዝባዊ የንቅናቄ መድረክ በጌዴኦ ዞን ገደብ ከተማ እየተካሄደ ነው።
በመድረኩ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተርና የዕለቱ የክብር እንግዳ ዶ/ር መሪሁን ፍቅሩ የንቅናቄ መድረኩ ዋና ዓላማ በሀገር ልማት ዕድገት ውስጥ የከተማና ከተሜነት ድርሻን ማሳደግ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
የከተሞችን የልማትና መልካም አስተዳደር ችግሮችን በመፍታት የህብረተሰቡን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ከማረጋገጥ አኳያ ውይይቱ ከፍተኛ ጠቀሜታ ያለው መሆኑን የከተማው ከንቲባ አቶ ታሪኩ ሮቤ አስረድተዋል፡፡
በንቅናቄ መድረኩ ከከተማ ቀበሌያት የተወጣጡ የግሉ ዘርፍ ባለሀብቶች፣ የንግዱ ማህበረሰብ፣ የመንግስት ሰራተኞች፣ የሀይማኖች አባቶች፣ የባህል ሽማግለዎች እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እየተሳተፉ ይገኛሉ፡፡
ዘጋቢ፡ ሳሙኤል በቀለ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
የሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ በስፖርትና ባህል ልማት ዘርፍ የሚገኘውን ተጠቃሚነት ለማሳደግ አበክሮ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
ህግና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን ፍትህ ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት ሥራ አፈፃፀም አደመጠ
ከተማዋን ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ እንደሚሠራ የዲላ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ