በልማትና መልካም አስተዳደር ችግሮች ዙሪያ የሚመክር ክልል አቀፍ የከተሞች ህዝባዊ የንቅናቄ መድረክ እየተካሄደ ነው
ሀዋሳ፡ ሕዳር 11/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በልማትና መልካም አስተዳደር ችግሮችና የመፍትሔ አቅጣጫዎች ዙሪያ የሚመክር ክልል አቀፍ የከተሞች ህዝባዊ የንቅናቄ መድረክ በጌዴኦ ዞን ገደብ ከተማ እየተካሄደ ነው።
በመድረኩ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተርና የዕለቱ የክብር እንግዳ ዶ/ር መሪሁን ፍቅሩ የንቅናቄ መድረኩ ዋና ዓላማ በሀገር ልማት ዕድገት ውስጥ የከተማና ከተሜነት ድርሻን ማሳደግ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
የከተሞችን የልማትና መልካም አስተዳደር ችግሮችን በመፍታት የህብረተሰቡን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ከማረጋገጥ አኳያ ውይይቱ ከፍተኛ ጠቀሜታ ያለው መሆኑን የከተማው ከንቲባ አቶ ታሪኩ ሮቤ አስረድተዋል፡፡
በንቅናቄ መድረኩ ከከተማ ቀበሌያት የተወጣጡ የግሉ ዘርፍ ባለሀብቶች፣ የንግዱ ማህበረሰብ፣ የመንግስት ሰራተኞች፣ የሀይማኖች አባቶች፣ የባህል ሽማግለዎች እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እየተሳተፉ ይገኛሉ፡፡
ዘጋቢ፡ ሳሙኤል በቀለ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
በግንቦት እና ሰኔ 2018 ዓ.ም ወራት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ፣ በቱሪዝም፣ በአረንጓዴ ዐሻራ፣ በዲጂታል ኢትዮጵያ፣ በሀገር በቀል ሪፎርም እና ቀጣናዊ ዲፕሎማሲ ዙሪያ ላይ ያተኮሩ የተለያዩ ከፍተኛ የሥራ ክንውኖችን አድርገዋል።
በህገወጥ መንገድ ከሀገር መውጣት ከህግ፣ ከደህንነት እና ከማህበራዊ አንፃር ከባድ ችግሮችን እንደሚያስከትል ተገለጸ
ወጣቶች ያላቸውን ጊዜ፣ እውቀትና ጉልበት በመጠቀም አቅመ ደካሞችንና የተቸገሩ ወገኖችን መደገፍ እንዳለባቸው ተገለፀ