የወላይታ ዞን ግብርና መምሪያ ወቅታዊ የግብርና ልማት ተግባራት ላይ ያተኮረ ዞናዊ ንቅናቄ መድረክ አካሄደ
የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጴጥሮስ ወ/ማርያም በንቅናቄው መድረክ ባስተላለፉት መልዕክት በግብርናው በሁሉም ዘረፍ የምርታማነት እምርታ ከፍ ለማድረግ በልዩ ትኩረት እንደሚሠራ ጠቁመዋል።
አክለው ለግብርናው ምርታማነት በቴክኖሎጂና በግብአት አጠቃቀም የተሻለ ለማድረግ ይሠራል ብለዋል።
በየወቅቱ የሚሠሩ የግብርና ሥራዎች ውጤታማ እንዲሆኑ በየዘርፉ ያለው ባለድርሻ አካላት ትኩረት እንዲሰጥ አሳስበዋል።
የዞኑ የግብርና መምሪያ ኃላፊ ዶ/ር ዳንኤል ደሌ እንደተናገሩት የግብርና ሥራዎችን በዘመናዊ መንገድ በማምረት ምርታማነት ለማሳደግ ክትትልና ድጋፍ እንደሚያሻ ጠቁመዋል።
በቀለች ጌቾ – ከዋካ ቅርንጫፍ

More Stories
የቅድመ በሽታ መከላከል ተግባራትን በአግባቡ በመፈፀም ጤናማ ትውልድ ለመፍጠር በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የሸዋል ዒድ (ቀሊ ፍቼ) ባህላዊ ስርዓት በስልጤ
ሁሉም ሰው ዴሞክራሲያዊ መብቱን ተጠቅሞ በቀጣይ የሚያስተዳድረውን መንግስት መምረጥ እንዲችል የምርጫ ካርድ በወቅቱ መያዝ እንደሚጠበቅበት ተገለጸ