የወላይታ ዞን ግብርና መምሪያ ወቅታዊ የግብርና ልማት ተግባራት ላይ ያተኮረ ዞናዊ ንቅናቄ መድረክ አካሄደ
የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጴጥሮስ ወ/ማርያም በንቅናቄው መድረክ ባስተላለፉት መልዕክት በግብርናው በሁሉም ዘረፍ የምርታማነት እምርታ ከፍ ለማድረግ በልዩ ትኩረት እንደሚሠራ ጠቁመዋል።
አክለው ለግብርናው ምርታማነት በቴክኖሎጂና በግብአት አጠቃቀም የተሻለ ለማድረግ ይሠራል ብለዋል።
በየወቅቱ የሚሠሩ የግብርና ሥራዎች ውጤታማ እንዲሆኑ በየዘርፉ ያለው ባለድርሻ አካላት ትኩረት እንዲሰጥ አሳስበዋል።
የዞኑ የግብርና መምሪያ ኃላፊ ዶ/ር ዳንኤል ደሌ እንደተናገሩት የግብርና ሥራዎችን በዘመናዊ መንገድ በማምረት ምርታማነት ለማሳደግ ክትትልና ድጋፍ እንደሚያሻ ጠቁመዋል።
በቀለች ጌቾ – ከዋካ ቅርንጫፍ
More Stories
ጥራት ያለው የጤና አገልግሎትን ለማህበረሰቡ ተደራሽ ለማድረግ የጤና ባለሙያዎች በኃላፊነት ሊሰሩ እንደሚገባ በጌዴኦ ዞን የይርጋጨፌ ወረዳ አስተዳደር አስታወቀ
የባስኬቶ ዞን ተወላጆች የአንድነት መድረክ ማጠቃለያ እየተካሄደ ነው
በእንስሳት እርባታ ከተሰማራን ወዲህ ኑሯችን ተሻሽሏል – የጋዘር ከተማ ወጣቶች