የወላይታ ዞን ግብርና መምሪያ ወቅታዊ የግብርና ልማት ተግባራት ላይ ያተኮረ ዞናዊ ንቅናቄ መድረክ አካሄደ
የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጴጥሮስ ወ/ማርያም በንቅናቄው መድረክ ባስተላለፉት መልዕክት በግብርናው በሁሉም ዘረፍ የምርታማነት እምርታ ከፍ ለማድረግ በልዩ ትኩረት እንደሚሠራ ጠቁመዋል።
አክለው ለግብርናው ምርታማነት በቴክኖሎጂና በግብአት አጠቃቀም የተሻለ ለማድረግ ይሠራል ብለዋል።
በየወቅቱ የሚሠሩ የግብርና ሥራዎች ውጤታማ እንዲሆኑ በየዘርፉ ያለው ባለድርሻ አካላት ትኩረት እንዲሰጥ አሳስበዋል።
የዞኑ የግብርና መምሪያ ኃላፊ ዶ/ር ዳንኤል ደሌ እንደተናገሩት የግብርና ሥራዎችን በዘመናዊ መንገድ በማምረት ምርታማነት ለማሳደግ ክትትልና ድጋፍ እንደሚያሻ ጠቁመዋል።
በቀለች ጌቾ – ከዋካ ቅርንጫፍ

More Stories
በጎፋ ዞን የዑባ ደብረፀሐይ ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ፓርቲውን በሀብት ለማጠናከር ከ1 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር በላይ የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ
የጓሮ አትክልትና የተለያዩ ሰብሎችን በማልማት የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ መቻላቸውን በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የሶያሜ ቀበሌ አርሶአደሮች ተናገሩ
በከተማው በተያዘው በጀት ዓመት በ5 ወራት ውስጥ 1 ቢሊየን 5 ሚሊዮን ብር ገቢ መሰብሰብ መቻሉን የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ አስታወቀ