የወላይታ ዞን ግብርና መምሪያ ወቅታዊ የግብርና ልማት ተግባራት ላይ ያተኮረ ዞናዊ ንቅናቄ መድረክ አካሄደ
የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጴጥሮስ ወ/ማርያም በንቅናቄው መድረክ ባስተላለፉት መልዕክት በግብርናው በሁሉም ዘረፍ የምርታማነት እምርታ ከፍ ለማድረግ በልዩ ትኩረት እንደሚሠራ ጠቁመዋል።
አክለው ለግብርናው ምርታማነት በቴክኖሎጂና በግብአት አጠቃቀም የተሻለ ለማድረግ ይሠራል ብለዋል።
በየወቅቱ የሚሠሩ የግብርና ሥራዎች ውጤታማ እንዲሆኑ በየዘርፉ ያለው ባለድርሻ አካላት ትኩረት እንዲሰጥ አሳስበዋል።
የዞኑ የግብርና መምሪያ ኃላፊ ዶ/ር ዳንኤል ደሌ እንደተናገሩት የግብርና ሥራዎችን በዘመናዊ መንገድ በማምረት ምርታማነት ለማሳደግ ክትትልና ድጋፍ እንደሚያሻ ጠቁመዋል።
በቀለች ጌቾ – ከዋካ ቅርንጫፍ
More Stories
አካል ጉዳተኞች መብቶቻቸውና ጥቅሞቻቸውን ለማስጠበቅ በቅንጅትና በጥምረት መስራት እንደሚገባ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ገለፀ
አካባቢን በመጠበቅና በማጽዳት ምቹና ጽዱ ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት በማገዝ ሁሉም የድርሻውን ልወጣ እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር እንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ አሳሰቡ
ግለሰባዊ ነጠላ ትርክቶችን በጋራ በመታገል በመደመር እሳቤ ችግሮችን መፍታት እንደሚገባ ተገለጸ