ለ19ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን በዓል ተጓዦች አቀባበል ለማድረግ ተዘጋጅተናል- የሲዳማ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋንታዬ ከበደ
በክልሉ በሁሉም አከባቢዎች 19ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን በዓልን በድምቀት ለማክበር ቅድመ ዝግጅት መደረጉንም ተናግረዋል።
የዓሉን አከባበር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር በሀዋሳ ከተማ ውይይት ተደርጓል።
የክልሉ የምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ በዚህ ወቅት እንደገለፁት በዓሉ አንድነት እና ህብረ ብሄራዊነትን በሚያጠናክር መልኩ እንዲከበር የክልሉ መንግሥት ተዘጋጅቷል ነው ያሉት።
የበዓሉ አክባሪዎች የሲዳማ ክልልን በማቋረጥ ስያልፉ በመግብያና መተላለፊያ አከባቢዎች ለእንግዶች የሲዳማን ህዝብ እሴት በሚገልጽ መልኩ ደማቅ አቀባበል ይደረጋል ። ይሄን ተግባር ለማሳለጥም ሰባት ወረዳዎች እና ሶስት ዞኖች መዘጋጀታቸውም ተመልክቷል ።የተጓዦችን ደህንነት ለመጠበቅም የፀጥታ አካላትና ህብረተሰቡ በጋራ ይሰራሉ ።
በዓሉን በክልሉ በሁሉም ዞኖች ወረዳዎች በዓሉን በድምቀት ለማክበር ዝግጀት ተደርጓል ያሉት ዋና አፈ ጉባኤዋ የበጎ አድራጎት ስራዎች፣ የደም ልገሳ እና በስፖርታዊ ውድድሮች ዋና ዋና ተግባራት ናቸው።
የዘንድሮው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን በዓል “ሀገራዊ መግባባት ለኅብረ-ብሔራዊ አንድነት” በሚል መሪ ሐሳብ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አርባምንጭ ከተማ ይከበራል።
ዘጋቢ፡ ጀማል የሱፍ
More Stories
አካል ጉዳተኞች መብቶቻቸውና ጥቅሞቻቸውን ለማስጠበቅ በቅንጅትና በጥምረት መስራት እንደሚገባ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ገለፀ
አካባቢን በመጠበቅና በማጽዳት ምቹና ጽዱ ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት በማገዝ ሁሉም የድርሻውን ልወጣ እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር እንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ አሳሰቡ
ግለሰባዊ ነጠላ ትርክቶችን በጋራ በመታገል በመደመር እሳቤ ችግሮችን መፍታት እንደሚገባ ተገለጸ