ለ19ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን በዓል ተጓዦች አቀባበል ለማድረግ ተዘጋጅተናል- የሲዳማ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋንታዬ ከበደ
በክልሉ በሁሉም አከባቢዎች 19ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን በዓልን በድምቀት ለማክበር ቅድመ ዝግጅት መደረጉንም ተናግረዋል።
የዓሉን አከባበር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር በሀዋሳ ከተማ ውይይት ተደርጓል።
የክልሉ የምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ በዚህ ወቅት እንደገለፁት በዓሉ አንድነት እና ህብረ ብሄራዊነትን በሚያጠናክር መልኩ እንዲከበር የክልሉ መንግሥት ተዘጋጅቷል ነው ያሉት።
የበዓሉ አክባሪዎች የሲዳማ ክልልን በማቋረጥ ስያልፉ በመግብያና መተላለፊያ አከባቢዎች ለእንግዶች የሲዳማን ህዝብ እሴት በሚገልጽ መልኩ ደማቅ አቀባበል ይደረጋል ። ይሄን ተግባር ለማሳለጥም ሰባት ወረዳዎች እና ሶስት ዞኖች መዘጋጀታቸውም ተመልክቷል ።የተጓዦችን ደህንነት ለመጠበቅም የፀጥታ አካላትና ህብረተሰቡ በጋራ ይሰራሉ ።
በዓሉን በክልሉ በሁሉም ዞኖች ወረዳዎች በዓሉን በድምቀት ለማክበር ዝግጀት ተደርጓል ያሉት ዋና አፈ ጉባኤዋ የበጎ አድራጎት ስራዎች፣ የደም ልገሳ እና በስፖርታዊ ውድድሮች ዋና ዋና ተግባራት ናቸው።
የዘንድሮው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን በዓል “ሀገራዊ መግባባት ለኅብረ-ብሔራዊ አንድነት” በሚል መሪ ሐሳብ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አርባምንጭ ከተማ ይከበራል።
ዘጋቢ፡ ጀማል የሱፍ

More Stories
የሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ በስፖርትና ባህል ልማት ዘርፍ የሚገኘውን ተጠቃሚነት ለማሳደግ አበክሮ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
ህግና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን ፍትህ ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት ሥራ አፈፃፀም አደመጠ
ከተማዋን ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ እንደሚሠራ የዲላ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ