የአካባቢውን ማህበረሰብ መልካም ባህላዊ እሴቶች በማጎልበት ዘላቂ ሠላም ለማስፈን በየደረጃው በተቀናጀ አግባብ መስራት እንደሚያስፈልግ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት አስታወቀ
በክልሉ ደቡብ ኦሞ ዞን በስፋት አርብቶ አደሮች የሚኖሩበት አካባቢ በመሆኑ ከሕብረተሰቡ አኗኗር ጋር ተያይዞ የሚከሰቱ የፀጥታ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት የማህበረሰቡን ነባርና መልካም ባህላዊ እሴቶችን ማጎልበት ይገባል ያሉት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ወላይቴ ቢቶ ናቸው።
ሀላፊዋ አያይዘዉም በአካባቢው በተለያዩ ምክንያቶች ለሚነሱ የፀጥታ ችግሮች መፍትሔ ለመሻት ከተንዛዛ አሰራሮች በመላቀቅ ፈጣን ምላሽ መስጠት ተጨማሪ ችግር እንዳይከሰት ይረዳል ብለዋል።
የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ በበኩላቸው፤ ፀጥታን በማደፍረስ የገቢ ምንጭ የሚያደርጉ ጥቂት አመራሮችን በመለየትና ሠላምን ማስፈን የሁሉንም ብቁ ተሳትፎ ይጠይቃል ብለዋል።
ለፀጥታ ችግሮች መነሻ የሚሆኑ ምክንያቶችንና ወንጀለኞችን ከመቆጣጠር አኳያ ከጎሳ መሪዎችና ወጣቶች ጋር በመሆን በተከናወኑ ዘርፈ ብዙ ተግባራት አንፃራዊ ሠላም ማስፈን መቻሉን የዞኑ ሠላምና ፀጥታ መምሪያ ሀላፊ አቶ ጎላ ጉዳቦ እና በዞኑ የሳላማጎ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ኦሌሉ ቻርኒሌይ ገልጸዋል።
አመራሮቹ አክለውም ከማህበረሰቡ ጋር በመቀናጀት በአካባቢው ዘላቂ ሠላም ለማስፈን ቀጣይነት ያለው ሥራ እየተሰራ እንደሚገኝም አስረድተዋል።
ዘጋቢ፡ ዳኜ ጥላሁን – ከጂንካ ጣቢያችን
More Stories
አካል ጉዳተኞች መብቶቻቸውና ጥቅሞቻቸውን ለማስጠበቅ በቅንጅትና በጥምረት መስራት እንደሚገባ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ገለፀ
አካባቢን በመጠበቅና በማጽዳት ምቹና ጽዱ ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት በማገዝ ሁሉም የድርሻውን ልወጣ እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር እንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ አሳሰቡ
ግለሰባዊ ነጠላ ትርክቶችን በጋራ በመታገል በመደመር እሳቤ ችግሮችን መፍታት እንደሚገባ ተገለጸ