የአካባቢውን ማህበረሰብ መልካም ባህላዊ እሴቶች በማጎልበት ዘላቂ ሠላም ለማስፈን በየደረጃው በተቀናጀ አግባብ መስራት እንደሚያስፈልግ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት አስታወቀ
በክልሉ ደቡብ ኦሞ ዞን በስፋት አርብቶ አደሮች የሚኖሩበት አካባቢ በመሆኑ ከሕብረተሰቡ አኗኗር ጋር ተያይዞ የሚከሰቱ የፀጥታ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት የማህበረሰቡን ነባርና መልካም ባህላዊ እሴቶችን ማጎልበት ይገባል ያሉት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ወላይቴ ቢቶ ናቸው።
ሀላፊዋ አያይዘዉም በአካባቢው በተለያዩ ምክንያቶች ለሚነሱ የፀጥታ ችግሮች መፍትሔ ለመሻት ከተንዛዛ አሰራሮች በመላቀቅ ፈጣን ምላሽ መስጠት ተጨማሪ ችግር እንዳይከሰት ይረዳል ብለዋል።
የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ በበኩላቸው፤ ፀጥታን በማደፍረስ የገቢ ምንጭ የሚያደርጉ ጥቂት አመራሮችን በመለየትና ሠላምን ማስፈን የሁሉንም ብቁ ተሳትፎ ይጠይቃል ብለዋል።
ለፀጥታ ችግሮች መነሻ የሚሆኑ ምክንያቶችንና ወንጀለኞችን ከመቆጣጠር አኳያ ከጎሳ መሪዎችና ወጣቶች ጋር በመሆን በተከናወኑ ዘርፈ ብዙ ተግባራት አንፃራዊ ሠላም ማስፈን መቻሉን የዞኑ ሠላምና ፀጥታ መምሪያ ሀላፊ አቶ ጎላ ጉዳቦ እና በዞኑ የሳላማጎ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ኦሌሉ ቻርኒሌይ ገልጸዋል።
አመራሮቹ አክለውም ከማህበረሰቡ ጋር በመቀናጀት በአካባቢው ዘላቂ ሠላም ለማስፈን ቀጣይነት ያለው ሥራ እየተሰራ እንደሚገኝም አስረድተዋል።
ዘጋቢ፡ ዳኜ ጥላሁን – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
የቅድመ በሽታ መከላከል ተግባራትን በአግባቡ በመፈፀም ጤናማ ትውልድ ለመፍጠር በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የሸዋል ዒድ (ቀሊ ፍቼ) ባህላዊ ስርዓት በስልጤ
ሁሉም ሰው ዴሞክራሲያዊ መብቱን ተጠቅሞ በቀጣይ የሚያስተዳድረውን መንግስት መምረጥ እንዲችል የምርጫ ካርድ በወቅቱ መያዝ እንደሚጠበቅበት ተገለጸ