በምክክር መድረኩ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አቡቶ አኒቶ፣ የርዕሰ መስተዳድሩ ልዩ አማካሪ አቶ ንጉሴ አስረስ፣ የብሄረሰቦች ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ አቶ ገመቹ አረቦ፣ የፕላንና ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ባዩሽ ተስፋ፣ የዞን እና ልዩ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በመሳተፍ ላይ ናቸው።
የመክፈቻው ንግግር ያደረጉት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አቡቶ አኒቶ፤ የመድረኩ ዓላማ የህዝቦችን ፍትሃዊ ተጠቃሚነትና ተደራሽነትን በማረጋገጥ እኩል ተጠቃሚነት ለማስፈን እንደሆነ ተናግረዋል።
ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ሳይረጋገጥ ጠንካራ ሀገረ-መንግስት መገንባት አዳጋች ነው ያሉት ዋና አፈ ጉባኤው፤ ከድጎማ በጀት ግልፀኝነት እንዲሁም ከአሳታፊነት ጋር ተያይዞ የሚታዩ ክፍተቶችን መቅረፍ ይገባል ብለዋል።
በመድረኩ የመወያያ ሰነድ ለውይይት ይቀርባል ተብሎ ይጠበቃል።
ዘጋቢ: ሄኖስ ካሳ – ከሆሳዕና ጣቢያችን
More Stories
የክልሉ መንግስት ከምን ጊዜም በላይ ህዝቡን ለማገልገል ዝግጁ ነው -ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር)
የጎፋ ዞን ሕዝብ ምክር ቤት 4ኛ ዙር መርሃ-ግብር 12ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 10ኛ መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ይገኛል
ከ19ሺህ በላይ ወጣቶች ቋሚና ጊዜያዊ የስራ ዕድል ተፈጥሮላቸው ወደ ተግባር መግባታቸውን ተገለጸ