በምክክር መድረኩ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አቡቶ አኒቶ፣ የርዕሰ መስተዳድሩ ልዩ አማካሪ አቶ ንጉሴ አስረስ፣ የብሄረሰቦች ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ አቶ ገመቹ አረቦ፣ የፕላንና ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ባዩሽ ተስፋ፣ የዞን እና ልዩ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በመሳተፍ ላይ ናቸው።
የመክፈቻው ንግግር ያደረጉት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አቡቶ አኒቶ፤ የመድረኩ ዓላማ የህዝቦችን ፍትሃዊ ተጠቃሚነትና ተደራሽነትን በማረጋገጥ እኩል ተጠቃሚነት ለማስፈን እንደሆነ ተናግረዋል።
ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ሳይረጋገጥ ጠንካራ ሀገረ-መንግስት መገንባት አዳጋች ነው ያሉት ዋና አፈ ጉባኤው፤ ከድጎማ በጀት ግልፀኝነት እንዲሁም ከአሳታፊነት ጋር ተያይዞ የሚታዩ ክፍተቶችን መቅረፍ ይገባል ብለዋል።
በመድረኩ የመወያያ ሰነድ ለውይይት ይቀርባል ተብሎ ይጠበቃል።
ዘጋቢ: ሄኖስ ካሳ – ከሆሳዕና ጣቢያችን
More Stories
ዲጂታል ኢትዮጵያን የመፍጠሪያ ጊዜን በማፋጠን ኢትዮጵያን የመጪው ዘመን መሪ ለማድረግ በትኩረት መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
የሆሳዕና እናት ቃለ ህይወት ቤተክርስቲያን አዲሱን ዓመት ምክንያት በማድረግ ከአንድ መቶ በላይ ለሚሆኑ አቅመ ደካሞች የምግብ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገች
እመርታ ለዘላቂ ከፍታ!