በምክክር መድረኩ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አቡቶ አኒቶ፣ የርዕሰ መስተዳድሩ ልዩ አማካሪ አቶ ንጉሴ አስረስ፣ የብሄረሰቦች ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ አቶ ገመቹ አረቦ፣ የፕላንና ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ባዩሽ ተስፋ፣ የዞን እና ልዩ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በመሳተፍ ላይ ናቸው።
የመክፈቻው ንግግር ያደረጉት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አቡቶ አኒቶ፤ የመድረኩ ዓላማ የህዝቦችን ፍትሃዊ ተጠቃሚነትና ተደራሽነትን በማረጋገጥ እኩል ተጠቃሚነት ለማስፈን እንደሆነ ተናግረዋል።
ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ሳይረጋገጥ ጠንካራ ሀገረ-መንግስት መገንባት አዳጋች ነው ያሉት ዋና አፈ ጉባኤው፤ ከድጎማ በጀት ግልፀኝነት እንዲሁም ከአሳታፊነት ጋር ተያይዞ የሚታዩ ክፍተቶችን መቅረፍ ይገባል ብለዋል።
በመድረኩ የመወያያ ሰነድ ለውይይት ይቀርባል ተብሎ ይጠበቃል።
ዘጋቢ: ሄኖስ ካሳ – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
በግንቦት እና ሰኔ 2018 ዓ.ም ወራት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ፣ በቱሪዝም፣ በአረንጓዴ ዐሻራ፣ በዲጂታል ኢትዮጵያ፣ በሀገር በቀል ሪፎርም እና ቀጣናዊ ዲፕሎማሲ ዙሪያ ላይ ያተኮሩ የተለያዩ ከፍተኛ የሥራ ክንውኖችን አድርገዋል።
በህገወጥ መንገድ ከሀገር መውጣት ከህግ፣ ከደህንነት እና ከማህበራዊ አንፃር ከባድ ችግሮችን እንደሚያስከትል ተገለጸ
ወጣቶች ያላቸውን ጊዜ፣ እውቀትና ጉልበት በመጠቀም አቅመ ደካሞችንና የተቸገሩ ወገኖችን መደገፍ እንዳለባቸው ተገለፀ