በምክክር መድረኩ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አቡቶ አኒቶ፣ የርዕሰ መስተዳድሩ ልዩ አማካሪ አቶ ንጉሴ አስረስ፣ የብሄረሰቦች ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ አቶ ገመቹ አረቦ፣ የፕላንና ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ባዩሽ ተስፋ፣ የዞን እና ልዩ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በመሳተፍ ላይ ናቸው።
የመክፈቻው ንግግር ያደረጉት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አቡቶ አኒቶ፤ የመድረኩ ዓላማ የህዝቦችን ፍትሃዊ ተጠቃሚነትና ተደራሽነትን በማረጋገጥ እኩል ተጠቃሚነት ለማስፈን እንደሆነ ተናግረዋል።
ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ሳይረጋገጥ ጠንካራ ሀገረ-መንግስት መገንባት አዳጋች ነው ያሉት ዋና አፈ ጉባኤው፤ ከድጎማ በጀት ግልፀኝነት እንዲሁም ከአሳታፊነት ጋር ተያይዞ የሚታዩ ክፍተቶችን መቅረፍ ይገባል ብለዋል።
በመድረኩ የመወያያ ሰነድ ለውይይት ይቀርባል ተብሎ ይጠበቃል።
ዘጋቢ: ሄኖስ ካሳ – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
የሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ በስፖርትና ባህል ልማት ዘርፍ የሚገኘውን ተጠቃሚነት ለማሳደግ አበክሮ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
ህግና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን ፍትህ ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት ሥራ አፈፃፀም አደመጠ
ከተማዋን ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ እንደሚሠራ የዲላ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ