የፊታችን ቅዳሜ በይፋ የሚመሰረተው ይኸው የዋካ ከተማ አስተዳደር፤ የዘመናት የህብረተሰቡ ጥያቄ ሆኖ የቆየ ሲሆን ጥያቄው አሁን ምላሽ በማግኘቱ መርካታቸውን ነዋሪዎቿ ተናግረዋል።
ከተማዋ እንደቀደምትነቷ ያለማደጓን አክለው የገለጹት ነዋሪዎቹ፣ ከተማዋን ካለችበት ደረጃ ከፍ በማድረግ ለማልማት እየተደረገ ያለውን ጥረት በእውቀት፣ በገንዘብና በጉልበት ለመደገፍ ቁርጠኞች ስለመሆናቸውም አረጋግጠዋል።
ምስረታውን ተንተርሶ ወደ ከተማዋ የሚመጡት እንግዶችን ለመቀበል ከወዲሁ ዝግጅት ማድረጋቸውንም ነዋሪዎቹ አስረድተዋል።
ዘጋቢ፡ አሸናፊ ግዘው – ከዋካ ጣቢያችን

 
                 
                                         
                                         
                                         
                                        
More Stories
የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶችን የስነ ተዋልዶ ጤና ችግሮች ለመቅረፍ የተጀመሩ ጥረቶችን ለማጎልበት የጤና አደረጃጀቶችን ሚና ማሳደግ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመግባት ዕድል ያገኙ ተማሪዎች የበለጠ ውጤታማ ለመሆን ትምህርታቸው ላይ ብቻ ሊያተኩሩ እንደሚገባ መልዕክት ተላለፈ
የሀዲያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለ2018 በጀት ዓመት ከ10 ቢልዮን ብር በላይ በጀት ለተለያዩ የልማት ስራዎች እንዲውል በተገቢው እንደሚሠራ ገለፀ