የፊታችን ቅዳሜ በይፋ የሚመሰረተው ይኸው የዋካ ከተማ አስተዳደር፤ የዘመናት የህብረተሰቡ ጥያቄ ሆኖ የቆየ ሲሆን ጥያቄው አሁን ምላሽ በማግኘቱ መርካታቸውን ነዋሪዎቿ ተናግረዋል።
ከተማዋ እንደቀደምትነቷ ያለማደጓን አክለው የገለጹት ነዋሪዎቹ፣ ከተማዋን ካለችበት ደረጃ ከፍ በማድረግ ለማልማት እየተደረገ ያለውን ጥረት በእውቀት፣ በገንዘብና በጉልበት ለመደገፍ ቁርጠኞች ስለመሆናቸውም አረጋግጠዋል።
ምስረታውን ተንተርሶ ወደ ከተማዋ የሚመጡት እንግዶችን ለመቀበል ከወዲሁ ዝግጅት ማድረጋቸውንም ነዋሪዎቹ አስረድተዋል።
ዘጋቢ፡ አሸናፊ ግዘው – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
ህብር ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የምርጫ ማኒፌስቶ፣ የዕጩ ማስተዋወቂያ እንዲሁም የምርጫ ቅስቀሳ ፕሮግራም በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ አካሄደ
ኦርቢስ ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ ጥራት ያለው የአይን ህክምና በሀገሪቱ ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየሰራ መሆኑ ተገለፀ
ብልጽግና ፓርቲ የማህበረሰቡ ችግር የሚቀርፉ ፕሮጀክቶችን ገንብቶ በማጠናቀቅ በውጤታማነት ለአገልግሎት እያበቃ ነው – ዶ/ር መሀመድ ኑርዬ