የፊታችን ቅዳሜ በይፋ የሚመሰረተው ይኸው የዋካ ከተማ አስተዳደር፤ የዘመናት የህብረተሰቡ ጥያቄ ሆኖ የቆየ ሲሆን ጥያቄው አሁን ምላሽ በማግኘቱ መርካታቸውን ነዋሪዎቿ ተናግረዋል።
ከተማዋ እንደቀደምትነቷ ያለማደጓን አክለው የገለጹት ነዋሪዎቹ፣ ከተማዋን ካለችበት ደረጃ ከፍ በማድረግ ለማልማት እየተደረገ ያለውን ጥረት በእውቀት፣ በገንዘብና በጉልበት ለመደገፍ ቁርጠኞች ስለመሆናቸውም አረጋግጠዋል።
ምስረታውን ተንተርሶ ወደ ከተማዋ የሚመጡት እንግዶችን ለመቀበል ከወዲሁ ዝግጅት ማድረጋቸውንም ነዋሪዎቹ አስረድተዋል።
ዘጋቢ፡ አሸናፊ ግዘው – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
በስራ ቦታቸው ላይ የህፃናት ማቆያ ማዕከል መቋቋሙ ስራቸውን በአግባቡ ለማከናወን እንዳስቻላቸው የማእከሉ ተጠቃሚ እናቶች ገለፁ
ለግብርናው እድገት መንግስት ከሚያደርገው ጥረት ጎን ለጎን የግብርና አጋር አካላት ድጋፍ የማይተካ ሚና እንዳለው የጎፋ ዞን ግብርና መምሪያ ገለጸ
በዳውሮ ዞን ታርጫ ከተማ የጥምቀት በዓል በተለያዩ ሀይማኖታዊ ክዋኔዎች በድምቀት ተከብሯል