የፊታችን ቅዳሜ በይፋ የሚመሰረተው ይኸው የዋካ ከተማ አስተዳደር፤ የዘመናት የህብረተሰቡ ጥያቄ ሆኖ የቆየ ሲሆን ጥያቄው አሁን ምላሽ በማግኘቱ መርካታቸውን ነዋሪዎቿ ተናግረዋል።
ከተማዋ እንደቀደምትነቷ ያለማደጓን አክለው የገለጹት ነዋሪዎቹ፣ ከተማዋን ካለችበት ደረጃ ከፍ በማድረግ ለማልማት እየተደረገ ያለውን ጥረት በእውቀት፣ በገንዘብና በጉልበት ለመደገፍ ቁርጠኞች ስለመሆናቸውም አረጋግጠዋል።
ምስረታውን ተንተርሶ ወደ ከተማዋ የሚመጡት እንግዶችን ለመቀበል ከወዲሁ ዝግጅት ማድረጋቸውንም ነዋሪዎቹ አስረድተዋል።
ዘጋቢ፡ አሸናፊ ግዘው – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
የጉራጌ ዞን ትምህርት መምሪያ የ2018 ዓ.ም የክረምት ወራት የትምህርት ቅድመ ዝግጅት ስራዎች ግምገማ እና የ2019 ዓ.ም የተማሪዎች ቅበላ የንቅናቄ መድረክ እየተካሄደ ነው
የዳውሮ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 13ኛ ሥራ ዘመን 29ኛ መደበኛ ጉባዔ መካሄድ ጀመረ
የህግ ታራሚዎችን አምራች ዜጋ ለማድረግ የስነ-ልቦና ድጋፍና የክህሎት ማጎልበቻ ስራዎች ወሳኝ መሆናቸው ተገለጸ