በፍርድ ቤቶችና በፍትህ ዘርፉ የሚታዩ የአገልግሎት ጥራትና የስነ-ምግባር ችግሮችን ለመቅረፍ በቅንጅት መስራት ይገባቸዋል – ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ
ሀዋሳ፡ ሕዳር 04/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በፍርድ ቤቶችና በፍትህ ዘርፉ የሚታዩ የአገልግሎት ጥራትና የስነ-ምግባር ችግሮችን ለመቅረፍ በቅንጅት መስራት እንደሚገባቸው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ ገለፁ።
በክልሉ የፍትህ አሰጣጥን ለማሻሻል እየተደረገ ባለው የምክክር መድረክ ንግግር ያደረጉት አፈ ጉባኤዋ የፍትህ ተቋማት ቅንጅታዊ አሰራር ውስን መሆን የህዝቦችን የፍትህ እርካታ እውን እንዳይሆን አድርጓል ብለዋል።
እንደ ሀገርም ዘርፉን ለማዘመን ባለፈው አንድ አመት ፍኖተ ካርታ ተቀርጾ እየተሰራ ቢሆንም የስነ-ምግባርና የገለልተኝነት ችግሮች አሁንም ስራ የሚጠይቁ ስለመሆናቸው አንስተዋል።
የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ኤርሴኖ አቡሬ፤ የተፈጠረው መድረክ ፍርድ ቤቱ ገለልተኝነቱን በጠበቀ መልኩ ከፍትህ ተቋማት ጋር ተቀናጅቶ እንዲሰራ አስቻይ ነው ብለዋል።
በተለይም ህግና ስርዓትን በተፃረረ መልኩ የሚሰሩ አካላትን ተጠያቂ ለማድረግና የጠራ አቋምን ይዞ ለመሄድ ቅንጅታዊ ስራዎች ይጠይቃሉ ብለዋል።
የፍትህ አሰጣጡን ለማዘመን የዲጂታል(በቴክኖሎጂ የታገዘ) የዳኝነት ስርዓት እየተዘረጋ ስለመሆኑም ተመላክቷል።
ዘጋቢ፡ ባዬ በልስቲ
More Stories
“አንድነታችንን በማጎልበት የህዝብ ጥቅም የሚያስቀድም ፖለቲካ ማራመድ ይጠበቅብናል” ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ
የሕብረ-ብሔራዊ አንድነት መጠናከር መሰረት የሆነው ብዝሃነትን በአግባቡ የማስተናገድ ሂደት ዘርፈ ብዙ ፋይዳ ያለው መሆኑ ተገለፀ
በክረምቱ ወራት ሊከሰቱ የሚችሉ የተለያዩ አደጋዎችን ለመከላከል አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ላይ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ገለጸ