በፍርድ ቤቶችና በፍትህ ዘርፉ የሚታዩ የአገልግሎት ጥራትና የስነ-ምግባር ችግሮችን ለመቅረፍ በቅንጅት መስራት ይገባቸዋል – ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ
ሀዋሳ፡ ሕዳር 04/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በፍርድ ቤቶችና በፍትህ ዘርፉ የሚታዩ የአገልግሎት ጥራትና የስነ-ምግባር ችግሮችን ለመቅረፍ በቅንጅት መስራት እንደሚገባቸው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ ገለፁ።
በክልሉ የፍትህ አሰጣጥን ለማሻሻል እየተደረገ ባለው የምክክር መድረክ ንግግር ያደረጉት አፈ ጉባኤዋ የፍትህ ተቋማት ቅንጅታዊ አሰራር ውስን መሆን የህዝቦችን የፍትህ እርካታ እውን እንዳይሆን አድርጓል ብለዋል።
እንደ ሀገርም ዘርፉን ለማዘመን ባለፈው አንድ አመት ፍኖተ ካርታ ተቀርጾ እየተሰራ ቢሆንም የስነ-ምግባርና የገለልተኝነት ችግሮች አሁንም ስራ የሚጠይቁ ስለመሆናቸው አንስተዋል።
የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ኤርሴኖ አቡሬ፤ የተፈጠረው መድረክ ፍርድ ቤቱ ገለልተኝነቱን በጠበቀ መልኩ ከፍትህ ተቋማት ጋር ተቀናጅቶ እንዲሰራ አስቻይ ነው ብለዋል።
በተለይም ህግና ስርዓትን በተፃረረ መልኩ የሚሰሩ አካላትን ተጠያቂ ለማድረግና የጠራ አቋምን ይዞ ለመሄድ ቅንጅታዊ ስራዎች ይጠይቃሉ ብለዋል።
የፍትህ አሰጣጡን ለማዘመን የዲጂታል(በቴክኖሎጂ የታገዘ) የዳኝነት ስርዓት እየተዘረጋ ስለመሆኑም ተመላክቷል።
ዘጋቢ፡ ባዬ በልስቲ

More Stories
ህዝበ ሙስሊሙ የመውሊድ በዓልን ሲያከብር በብዝሃነት ውስጥ የሚንፀባረቁ የመረዳዳትና የአብሮነት በጎ እሴቶችን ይበልጥ በማጠናከር ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ኃላፊና የየዞን ከፍተኛ አመራሮች በሣውላ ማረሚያ ተቋም አረንጓዴ አሻራቸውን በማኖር ልዩ ልዩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ
በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር ምርመራ እና ልየታ ተካሄደ