የትራፊክ አደጋን ለመከላከል በህብረተሰቡ ዘንድ በጎ ተፅእኖን መፍጠር ከሚችሉ ግለሰቦች ጋር የሚሠሩ ሥራዎች የሚበረታቱ እንደሆነ ተገለፀ
ሀዋሳ፡ ሕዳር 03/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የትራፊክ አደጋን ለመከላከል በህብረተሰቡ ዘንድ በጎ ተፅእኖን መፍጠር ከሚችሉ ግለሰቦች ጋር የሚሠሩ ሥራዎች የሚበረታቱ እንደሆነ ተገለፀ፡፡
ከጊዜ ወደ ጊዜ ገዳይነቱና ጎጂነቱ እየጨመረ የመጣውን የትራፊክ አደጋን ለመቀነስ እንዲሁም ስለ መንገድ ደህንነት ግንዛቤን ለመጨመር የሚረዱ ተግባራት በጌዴኦ ዞን የተለያዩ ከተሞች ላይ ተከናውነዋል፡፡
የዲላ ከተማ የትራፊክ ፖሊስ አስተባባሪ ኢንስፔክተር ሀብታሙ ህርባዬ እንደተናገሩት፤ በዲላ ከተማ ከታዋቂ ግለሰቦች ጋር ስለ ትራፊክ አደጋ ግንዛቤ ለመፍጠር የተደረገው ተግባር በሚገባ የሚያግዝ ነው፡፡
ታዋቂ ግለሰቦች ስለ ትራፊክ አደጋ አስከፊነት ለማህበረሰቡ ለማስገንዘብ ስላደረጉት ትብብርም ከልባቸው አመስግነዋል፡፡
ከዋና ሥራው ባሻገር በበጎ ተግባሩና በሰብዓዊ ሥራ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ መልካም ተፅእኖን መፍጠር የቻለው የይርጋጨፌ ከተማ የትራፊክ ፖሊስ አባል ሳጅን መልካሙ በየነ እንደተናገሩት፤ ታዋቂ ግለሰቦች ሥራዬን ለማገዝ ብለው ይርጋጨፌ ከተማ ላይ መገኘታቸው ለሥራዬ ተጨማሪ ሞራል ሆኖኛል፡፡
የገደብ ከተማ የትራፊክ ፖሊስ አስተባባሪ ምክትል ኢንስፔክተር ዳዊት ደግፌ በበኩላቸው፤ ዋናው መንገድ ከተማውን ለሁለት አቋርጦ የሚያልፍ በመሆኑና ከተማው በርካታ የሁለት እግር ሞተር ሳይክል የሚገኝበት እንደመሆኑ መሠል ሥራዎች አደጋውን ለመቀነስ አስተዋፅኦው ከፍተኛ ነው ብለዋል፡፡
አደራጅ ዘሪሁን ማስታወቂያና መድረክ ሥራ ከጌዴኦ ዞን አስተዳደርና ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ጋር በመተባበር ባዘጋጀው መርሃ ግብር ላይ በርካታ አርቲስቶችና የማህበራዊ ሚዲያ አንቂዎች ተሳትፈዋል፡፡
ዘጋቢ፡ አብነት አበበ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
ህዝበ ሙስሊሙ የመውሊድ በዓልን ሲያከብር በብዝሃነት ውስጥ የሚንፀባረቁ የመረዳዳትና የአብሮነት በጎ እሴቶችን ይበልጥ በማጠናከር ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ኃላፊና የየዞን ከፍተኛ አመራሮች በሣውላ ማረሚያ ተቋም አረንጓዴ አሻራቸውን በማኖር ልዩ ልዩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ
በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር ምርመራ እና ልየታ ተካሄደ