በሱማሌ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት ሊበን ዞን 2 ሺህ ኪሎ ዋት ኃይል ማመንጨት የሚችል የቦቆሎማዮ ከተማ የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ተመረቀ
የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቱ ከ60 ሺህ በላይ ህዝብ የመብራት አገልግሎት ተጠቃሚ ማድረግ የሚችል ነው ተብሏል።
የፕሮጀክቱ አጠቃላይ ግንባታና ዝርጋታም ከ800 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ እንደወጣበት ተመላክቷል።
በሶማሌ ክልል ከተገነቡት የፀሐይ ኃይል ማመንጫዎች መካከል የቦቆሎማዮ ፕሮጀክት 4ኛው ሲሆን በግዝፈቱ በምሥራቅ አፍሪካ የመጀመሪያ እንደሆነም ተገልጿል።
አሁን ላይ ከ21 ኪሎ ሜትር በላይ የመስመር ዝርጋታና የ5 ትራንስፎርመር ተከለ ተጠናቅቋል።
በፕሮጀክቱ 8 ሺህ የቆጣሪ ደንበኞች ተጠቃሚ ይሆናሉ ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን ከቦቆሎማዮ ከተማ በተጨማሪ በአቅራቢያው የሚገኙ የስደተኞች ማረፊያ ካምፖችንም ጭምር የመብራት ተጠቃሚ ያደርጋል ተብሏል።
ከለውጡ ወዲህ በሱማሌ ክልል ያሉ 81 አዳዲስ ከተሞች የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተጠቃሚ መሆን መቻላቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሐመድ አስታውቀዋል።
በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ለይ የሱማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ መሀመድን ጨምሮ የኢፌዲሪ ውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ፣ የኢነርጂ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ፣ የኢትዮጵያ መብራት ኃይል አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጅነር ሽፈራው ተሊላ እንዲሁም የሶማሌ ክልል ሀገር ሽማግሌዎች እና የቦቆሎማዮ ከተማ ነዋሪዎች ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ ጌታሁን አንጭሶ

 
                 
                                         
                                         
                                         
                                        
More Stories
የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶችን የስነ ተዋልዶ ጤና ችግሮች ለመቅረፍ የተጀመሩ ጥረቶችን ለማጎልበት የጤና አደረጃጀቶችን ሚና ማሳደግ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመግባት ዕድል ያገኙ ተማሪዎች የበለጠ ውጤታማ ለመሆን ትምህርታቸው ላይ ብቻ ሊያተኩሩ እንደሚገባ መልዕክት ተላለፈ
የሀዲያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለ2018 በጀት ዓመት ከ10 ቢልዮን ብር በላይ በጀት ለተለያዩ የልማት ስራዎች እንዲውል በተገቢው እንደሚሠራ ገለፀ