የአራቱም ክልሎች የጋራ ሃብት የሆኑ የመንግስት የልማት ድርጅቶች አፈጻጸም እና አጠቃላይ ተቋማቱ ያሉበትን ደረጃ የሚገመግም የውይይት መድረክ እየተካሄደ ይገኛል
ሐዋሳ፣ ጥቅምት 27/02/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የደቡብ ኢትዮጵያ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ፣ የሲዳማ እና የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልሎች የጋራ ሃብት የሆኑ የመንግስት የልማት ድርጅቶች አፈጻጸምና አጠቃላይ ተቋማቱ ያሉበትን ደረጃ የሚገመግም የውይይት መድረክ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል፡፡
በቀድሞው የደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል መንግስት ተቋቁመው የነበሩ እና አራቱም ክልሎች ሲደራጁ የጋራ ሃብት ሆነው እንዲቀጥሉ የተወሰኑ የመንግስት የልማት ድርጅቶች ማለትም የደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት፣ የደቡብ ካፒታል አክስዮን ማህበር፣ የኦሞ ባንክ እንዲሁም ሴራዴፍ ኮርፖሬት አፈጻጸም ግምገማ የየክልሎቹ ርዕሰ መስተዳድራን፣ የልማት ድርጅቶቹ የስራ ኃላፊዎች እና የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ነው የውይይት መድረኩ እየተካሄደ ያለው፡፡
በውይይት መድረኩ የልማት ድርጅቶቹ በአፈጻጸም ያስመዘገቧቸውን ውጤቶች እና ያጋጠሟቸውን ተግዳሮቶች በመገምገም እንዲሁም በቀጣይ ትኩረት በሚሹ ጉዳዮች ላይ በመወያየት የጋራ አቅጣጫ ይቀመጣል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
More Stories
አካል ጉዳተኞች መብቶቻቸውና ጥቅሞቻቸውን ለማስጠበቅ በቅንጅትና በጥምረት መስራት እንደሚገባ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ገለፀ
አካባቢን በመጠበቅና በማጽዳት ምቹና ጽዱ ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት በማገዝ ሁሉም የድርሻውን ልወጣ እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር እንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ አሳሰቡ
ግለሰባዊ ነጠላ ትርክቶችን በጋራ በመታገል በመደመር እሳቤ ችግሮችን መፍታት እንደሚገባ ተገለጸ