የቢላሃሪዚያ እና አንጀት ጥገኛ ትላትሎች ማስወገጃ የማህበረሰብ አቀፍ መድኃኒት ዕደላ ዘመቻ ማስጀመሪያ የአመራር ግንዛቤ መፍጠሪያ መድረክ በአርባምንጭ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊና የህክምና ዘርፍ ኃላፊ አቶ ናፍቆት ብርሃኑ በመክፈቻ ንግግራቸው እንዳሉት፤ በተለይ ተጋላጭ ለሆኑ የክልሉ አካባቢዎች 1 ነጥብ 5 ሚሊየን ለሚሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች የመድኃኒት ዕደላ ዘመቻ ለማድረግ የቅድመ ዝግጅት ሥራ ተጠናቋል።
በመሆኑም ትኩረት የሚሹ ሐሩራማ በሽታዎችን ለመከላከል የባለድርሻ አካላት ቅንጅታዊ ሥራ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አሳስበዋል።
የዚህ መድረክ ዋና ዓላማውም ከህዳር ወር መጀመሪያ ጀምሮ የማህበረሰብ አቀፍ መድኃኒት ዕደላ የዘመቻ ሥራዎች በትኩረትና በጥራት ለመስራት እንደሆነም ተመላክቷል።
ትኩረት የሚሹ ሐሩራማ በሽታዎች፣ የአንጀት ጥገኛ ትላትሎችና የቢላሃሪዚያ በሽታዎች መከላከያ የማህበረሰብ አቀፍ የመድኃኒት ዕደላ የአመራር ግንዛቤ መፍጠሪያ መድረክ በአርባምንጭ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።
ዘጋቢ፡ ሰለሞን አላሶ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
በጎፋ ዞን የዑባ ደብረፀሐይ ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ፓርቲውን በሀብት ለማጠናከር ከ1 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር በላይ የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ
የጓሮ አትክልትና የተለያዩ ሰብሎችን በማልማት የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ መቻላቸውን በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የሶያሜ ቀበሌ አርሶአደሮች ተናገሩ
በከተማው በተያዘው በጀት ዓመት በ5 ወራት ውስጥ 1 ቢሊየን 5 ሚሊዮን ብር ገቢ መሰብሰብ መቻሉን የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ አስታወቀ