የቢላሃሪዚያ እና አንጀት ጥገኛ ትላትሎች ማስወገጃ የማህበረሰብ አቀፍ መድኃኒት ዕደላ ዘመቻ ማስጀመሪያ የአመራር ግንዛቤ መፍጠሪያ መድረክ በአርባምንጭ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊና የህክምና ዘርፍ ኃላፊ አቶ ናፍቆት ብርሃኑ በመክፈቻ ንግግራቸው እንዳሉት፤ በተለይ ተጋላጭ ለሆኑ የክልሉ አካባቢዎች 1 ነጥብ 5 ሚሊየን ለሚሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች የመድኃኒት ዕደላ ዘመቻ ለማድረግ የቅድመ ዝግጅት ሥራ ተጠናቋል።
በመሆኑም ትኩረት የሚሹ ሐሩራማ በሽታዎችን ለመከላከል የባለድርሻ አካላት ቅንጅታዊ ሥራ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አሳስበዋል።
የዚህ መድረክ ዋና ዓላማውም ከህዳር ወር መጀመሪያ ጀምሮ የማህበረሰብ አቀፍ መድኃኒት ዕደላ የዘመቻ ሥራዎች በትኩረትና በጥራት ለመስራት እንደሆነም ተመላክቷል።
ትኩረት የሚሹ ሐሩራማ በሽታዎች፣ የአንጀት ጥገኛ ትላትሎችና የቢላሃሪዚያ በሽታዎች መከላከያ የማህበረሰብ አቀፍ የመድኃኒት ዕደላ የአመራር ግንዛቤ መፍጠሪያ መድረክ በአርባምንጭ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።
ዘጋቢ፡ ሰለሞን አላሶ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
ህዝበ ሙስሊሙ የመውሊድ በዓልን ሲያከብር በብዝሃነት ውስጥ የሚንፀባረቁ የመረዳዳትና የአብሮነት በጎ እሴቶችን ይበልጥ በማጠናከር ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ኃላፊና የየዞን ከፍተኛ አመራሮች በሣውላ ማረሚያ ተቋም አረንጓዴ አሻራቸውን በማኖር ልዩ ልዩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ
በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር ምርመራ እና ልየታ ተካሄደ