“የህልም ጉልበት፤ ለእምርታዊ ዕድገት!!” ሀገራዊ ስልጠና አካል የሆነው በኣሪ ዞን ብልጽግና ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አስተባባሪነት ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቋል።
በነበረው ስልጠና አመራሩ የተሻለ አካባቢያዊ፣ ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ሁኔታዎችን እንዲገነዘቡ ተጠማሪ ግንዛቤን መፈጠሩን የኣሪ ዞን የመንግስት ዋና ተጠሪና ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ጉራልቅ ይዥማልቅ ገልፀዋል።
በየአካባቢው ያሉ ፀጋዎችን እንደምቹ አጋጋሚ በመጠቀም ሰፋፊ ልማቶችን ሕዝቡን በማቀናጀት ተግባራዊ ማድረግ የሰልጠኝ አመራር ቁልፍ ተግባር መሆን እንዳለበት አቶ ጉራልቅ አሳስበዋል።
የኣሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም አታ የነበረው ስልጠና የአመራሩ ክህሎት፣ ብቃትና ዕውቀቱ ከተግባር ጋር ተሰናስኖ መምራት የሚያስችል መልዕክት መተላለፉን አብራርተዋል።
ዛሬ ለነገ ለውጥ መነሻ በመሆኑ ነገን የተሻለች ዞን፣ ክልል ብሎም ሀገር ለማየት በቁርጠኝነትና በቁጭት አመራሩ በአንድ አሀድና አስተሳሰብ መሥራት ይጠበቅበታል ሲሉም አቶ አብርሃም አሳስበዋል።
በስልጠናው በነበራቸው ቆይታ ወጥ የሆነ ሀገራዊ አንድነትና እሳቤ ኖሮን የመምራት አቅማችንን እንዲናሳድግ ግንዛቤ መጨበጣቸውን ሰልጣኝ አመራሮች ገልፀዋል።
ይህንን ወደ ተግባር ለመቀየር የተሰጠንን ሀላፊነት ለመወጣት እንሠራለን ሲሉም አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
ስልጠናው በተሳካ መልኩ መልዕክት ተላልፎ የተቋጨ ሲሆን በቀጣይ የርዕሰ ጉዳይ ሐሳቡ በተዋረድ 4ኛና 5ኛ ዙር ድረስ እንደሚወርድም ታውቋል።
ዘጋቢ: ተመስገን አበራ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
ከመማር ማስተማር ተግባር ባለፈ የአካባቢ ማህበረሰብ ተጠቃሚነት ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን የሚዛን ግብርና ቴክኒክ ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጅ አስታወቀ
የኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ(ዶ/ር) መጭው ጊዜ ከተስፋ ብርሃን ወደሚጨበጥ ብርሃን የምንሸጋገርበት ብሩህ ዘመን መሆኑን ተናገሩ
በተቀሩት አጭር ቀናት ህብረተሠቡ የመራጭነት ካርዱን በመውሰድ የዜግነት ግዴታውን እንዲወጣ የጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ወረዳና አካባቢው የፌደራልና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ጥሪ አቀረቡ