የምክክር ሂደቱ በመከባበር እውነትን ባህል ያደረገ፣ መሰረታዊ የሀገሪቱን ችግሮች የሚገልፅ እና ኢትዮጵያን የሚመጥን መሆኑን የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶክተር ዮናስ አዳዬ ገለፁ።
ለ3 ቀናት ሲካሄድ የነበረው የአጀንዳ አሰባሰብ ሂደትና የተወካዮች መረጣ በስኬት ተጠናቋል።
የአጀንዳ እና የተወካይ መረጣው እውነትን መሰረት ያደረገ እና ሀገራዊ መግባባትን መፍጠር፣ በህዝብና በመንግስት መካከል እምነት እንዲፈጠር ማድረግ እና ምክክርን ባህል ማድረግን ያየንበት መድረክ ነው ብለዋል።
የሚዲያ ባለሙያዎችም እንደተመለከቱት የምክክር መድረኩ የአንድ ፓርቲ ብቻ ሳይሆን የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች የተሳተፉበት እና ለሀገር ሰላም መሰረት የሚጣልበት ነው ሲሉ ገልጸዋል።
ኮሚሽነሩ አክለውም በቀጣይ ከአርብ እስከ እሁድ በሚኖሩ ቀናት የተለያዩ የዩኒቨርስቲ ምሁራን፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሀይማኖት መሪዎች እና ተፅእኖ ፈጣሪዎች በራሳቸው ልምምድ የሚመክሩበት ብሎም አጀንዳ የሚመረጡበት መድረክ እንደሆነ አስታውቀዋል።
ባለፉት ቀናት በተደረገው የማህበረሰብ ውይይትም ሆነ በቀጣይ ቀናት በተፅእኖ ፈጣሪዎች የሚደረገው የምክክር መድረክ ዋና አላማው ሀገራዊ አጀንዳ ማቅረብ፣ በጥልቀት የመጣንበትን መንገድ መፈተሽ እና በሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የሚሳተፉ ተወካዮችን መምረጥ በመሆኑ በጥራት እንደሚካሄድ ነው ኮሚሽነሩ የገለፁት።
ለ3 ቀናት ሲካሄድ የነበረው የአጀንዳና የተወካይ መረጣ የተሳካ እንደሆነ ተመላክቷል።
ዘጋቢ፡ ገነት መኮንን – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
የፀረ-ተህዋስያን መድኃኒቶች በጀርሞች መላመድን ለመከላከል በሚደረገው አገራዊ ጥረት ውስጥ የሚዲያ ባለሙያዎች ግንባር ቀደም ሚና ሊጫወቱ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ገለጸ
መምህራን የሚገባቸውን ጥቅማ ጥቅምና መብት በማስጠበቅ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መምህራን ማህበር አስታወቀ
የልማትና መልካም አስተዳደር ተግባራትን ለማፋጠን ግብር ከፋዩ የሚጠበቅበትን ታክስ በወቅቱና በታማኝነት መክፈል እንዳለበት ተገለጸ