በጎፋ ዞን ሣውላ ከተማ የህልም ጉልበት ለእምርታዊ ዕድገት” በሚል ርዕስ የአቅም ግንባታ ስልጠና እየወሰዱ ያሉ የብልፅግና ፓርቲ አመራሮች በደንባ ጎፋ ወረዳ የዛንጋ ዶርማለ የወተት ላም እና የዙሉዚ ጺላ የፊዬል ማሞከት የተደራጁ ማህበራት የስራ እንቅስቃሴ እንዲሁም የእስፔ ዲቻ ህብረት ስራ ዩኒየን የመኖ ማቀነባበሪያ ጎብኝተዋል።
ሰልጠኝ አመራሮች በመስክ ምልከታ ባዩት ነገር መደሰታቸውን ገልፀው በቁርጠኝነት መሥራት ከተቻለ ከዚህ የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ እንደሚቻል ገልፀዋል።
የመስክ ምልከታዉ ሰልጣኞች ከንድፈ ሀሳብ ባሻገር ከተግባር ተሞክሮና ከልምድ መማማር የሚያስችል ፋይዳዉ የጎላ መሆኑን የደንባ ጎፋ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አንዳርጌ አራታ ገልጸዋል።
የጎፋ ዞን የመንግስት ዋና ተጠሪና የብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ታደለ ያዕቆብ ሰልጣኞች በንድፈ ሀሳብ ያገኙትን ዕውቀት ተጠቅመው እንደሀገር የተጀመረውን የሌማት ትሩፋት ፕሮግራም ውጤታማ ለማድረግ የበኩላቸውን ድርሻ ለመወጣት የመስክ ምልከታው አቅም እንደሚፈጥርላቸው ጠቁመዋል።
ዘጋቢ ፡ አይናለም ሰለሞን-ከሳውላ ጣቢያችን
More Stories
አካል ጉዳተኞች መብቶቻቸውና ጥቅሞቻቸውን ለማስጠበቅ በቅንጅትና በጥምረት መስራት እንደሚገባ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ገለፀ
አካባቢን በመጠበቅና በማጽዳት ምቹና ጽዱ ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት በማገዝ ሁሉም የድርሻውን ልወጣ እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር እንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ አሳሰቡ
ግለሰባዊ ነጠላ ትርክቶችን በጋራ በመታገል በመደመር እሳቤ ችግሮችን መፍታት እንደሚገባ ተገለጸ