በጎፋ ዞን ሣውላ ከተማ የህልም ጉልበት ለእምርታዊ ዕድገት” በሚል ርዕስ የአቅም ግንባታ ስልጠና እየወሰዱ ያሉ የብልፅግና ፓርቲ አመራሮች በደንባ ጎፋ ወረዳ የዛንጋ ዶርማለ የወተት ላም እና የዙሉዚ ጺላ የፊዬል ማሞከት የተደራጁ ማህበራት የስራ እንቅስቃሴ እንዲሁም የእስፔ ዲቻ ህብረት ስራ ዩኒየን የመኖ ማቀነባበሪያ ጎብኝተዋል።
ሰልጠኝ አመራሮች በመስክ ምልከታ ባዩት ነገር መደሰታቸውን ገልፀው በቁርጠኝነት መሥራት ከተቻለ ከዚህ የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ እንደሚቻል ገልፀዋል።
የመስክ ምልከታዉ ሰልጣኞች ከንድፈ ሀሳብ ባሻገር ከተግባር ተሞክሮና ከልምድ መማማር የሚያስችል ፋይዳዉ የጎላ መሆኑን የደንባ ጎፋ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አንዳርጌ አራታ ገልጸዋል።
የጎፋ ዞን የመንግስት ዋና ተጠሪና የብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ታደለ ያዕቆብ ሰልጣኞች በንድፈ ሀሳብ ያገኙትን ዕውቀት ተጠቅመው እንደሀገር የተጀመረውን የሌማት ትሩፋት ፕሮግራም ውጤታማ ለማድረግ የበኩላቸውን ድርሻ ለመወጣት የመስክ ምልከታው አቅም እንደሚፈጥርላቸው ጠቁመዋል።
ዘጋቢ ፡ አይናለም ሰለሞን-ከሳውላ ጣቢያችን
More Stories
በኢፌዴሪ የጤና ሚኒስትር ሚኒስቴር ዴኤታ ደረጄ ዱጉማ (ዶ/ር) የተመራ ልዑክ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በኣሪና ደቡብ ኦሞ ዞኖች የሥራ ጉብኝት አደረጉ
በህዳሴ ግድብ ግንባታ የታየው አንድነት እና ትብብር በልማቱ እና በሰላሙ ላይ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ተገለጸ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቡርጂ ዞን “በህብረት ችለናል” በሚል መሪ ቃል ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በድል ተጠናቆ መመረቁን አስመልክቶ ዞናዊ የፓናል ዉይይት መድረክ ተካሄደ