የአቅም ግንባታ ስልጠና እየወሰዱ ያሉ አመራሮች በሶዶ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል።
“የህልም ጉልበት ለእምርታዊ እድገት” በሚል ርዕስ በአቅም ግንባታ ስልጠና ላይ እየተሳተፉ ያሉ አመራሮች በሶዶ ከተማ የተሰሩ የተለያዩ ልማት ስራዎች ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
ሰልጣኞች በሶዶ ከተማ የሌማት ትሩፋትና በወጣቶች ስራ ዕድል ፈጠራ የተሰሩ የተለያዩ የልማት ስራዎችን ነው የጎበኙት።
ሠልጣኞች ከንድፈ ሀሳብ ባሻገር ልምድ ልውውጥ ማድረግ ፋይዳዉ ጉልህ ሚና እንዳለውም ተመላክቷል።
“የህልም ጉልበት ለእምርታዊ እድገት” በሚል ሀሳብ በወላይታ ዞን በየደረጃው የሚገኙ 1 ሺህ 5 መቶ የሚጠጉ አመራሮች በወላይታ ሶዶ ከተማ ስልጠናውን እየወሰዱ መሆናቸውን ይታወሳል።
ዘጋቢ ፡ በቀሌች ጌቾ -ከዋካ ቅርንጫፍ
More Stories
የኢፌዲሪ ውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሃ ፕሮጀክት ከ82 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ በጉራጌ ዞን ምሁር አክሊል ወረዳ መቆርቆር ቀበሌ ያስገነባው የንጹህ መጠ ውሃ ፕሮጀክት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ
የኡዱሂያ የዕርድ ስርዓት….የአብሮነት ነፀብራቅ
በቅርቡ በሚሰጠው የ6ኛ እና የ8ኛ ክልላዊ ፈተና ላይ ከ53 ሺህ በላይ ተማሪዎች ለፈተና እንደሚቀርቡ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሀዲያ ዞን ትምህርት መመሪያ አስታወቀ