የአቅም ግንባታ ስልጠና እየወሰዱ ያሉ አመራሮች በሶዶ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል።
“የህልም ጉልበት ለእምርታዊ እድገት” በሚል ርዕስ በአቅም ግንባታ ስልጠና ላይ እየተሳተፉ ያሉ አመራሮች በሶዶ ከተማ የተሰሩ የተለያዩ ልማት ስራዎች ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
ሰልጣኞች በሶዶ ከተማ የሌማት ትሩፋትና በወጣቶች ስራ ዕድል ፈጠራ የተሰሩ የተለያዩ የልማት ስራዎችን ነው የጎበኙት።
ሠልጣኞች ከንድፈ ሀሳብ ባሻገር ልምድ ልውውጥ ማድረግ ፋይዳዉ ጉልህ ሚና እንዳለውም ተመላክቷል።
“የህልም ጉልበት ለእምርታዊ እድገት” በሚል ሀሳብ በወላይታ ዞን በየደረጃው የሚገኙ 1 ሺህ 5 መቶ የሚጠጉ አመራሮች በወላይታ ሶዶ ከተማ ስልጠናውን እየወሰዱ መሆናቸውን ይታወሳል።
ዘጋቢ ፡ በቀሌች ጌቾ -ከዋካ ቅርንጫፍ

More Stories
ህብር ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የምርጫ ማኒፌስቶ፣ የዕጩ ማስተዋወቂያ እንዲሁም የምርጫ ቅስቀሳ ፕሮግራም በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ አካሄደ
ኦርቢስ ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ ጥራት ያለው የአይን ህክምና በሀገሪቱ ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየሰራ መሆኑ ተገለፀ
ብልጽግና ፓርቲ የማህበረሰቡ ችግር የሚቀርፉ ፕሮጀክቶችን ገንብቶ በማጠናቀቅ በውጤታማነት ለአገልግሎት እያበቃ ነው – ዶ/ር መሀመድ ኑርዬ