የአቅም ግንባታ ስልጠና እየወሰዱ ያሉ አመራሮች በሶዶ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል።
“የህልም ጉልበት ለእምርታዊ እድገት” በሚል ርዕስ በአቅም ግንባታ ስልጠና ላይ እየተሳተፉ ያሉ አመራሮች በሶዶ ከተማ የተሰሩ የተለያዩ ልማት ስራዎች ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
ሰልጣኞች በሶዶ ከተማ የሌማት ትሩፋትና በወጣቶች ስራ ዕድል ፈጠራ የተሰሩ የተለያዩ የልማት ስራዎችን ነው የጎበኙት።
ሠልጣኞች ከንድፈ ሀሳብ ባሻገር ልምድ ልውውጥ ማድረግ ፋይዳዉ ጉልህ ሚና እንዳለውም ተመላክቷል።
“የህልም ጉልበት ለእምርታዊ እድገት” በሚል ሀሳብ በወላይታ ዞን በየደረጃው የሚገኙ 1 ሺህ 5 መቶ የሚጠጉ አመራሮች በወላይታ ሶዶ ከተማ ስልጠናውን እየወሰዱ መሆናቸውን ይታወሳል።
ዘጋቢ ፡ በቀሌች ጌቾ -ከዋካ ቅርንጫፍ

More Stories
የሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ በስፖርትና ባህል ልማት ዘርፍ የሚገኘውን ተጠቃሚነት ለማሳደግ አበክሮ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
ህግና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን ፍትህ ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት ሥራ አፈፃፀም አደመጠ
ከተማዋን ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ እንደሚሠራ የዲላ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ