የአቅም ግንባታ ስልጠና እየወሰዱ ያሉ አመራሮች በሶዶ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል።
“የህልም ጉልበት ለእምርታዊ እድገት” በሚል ርዕስ በአቅም ግንባታ ስልጠና ላይ እየተሳተፉ ያሉ አመራሮች በሶዶ ከተማ የተሰሩ የተለያዩ ልማት ስራዎች ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
ሰልጣኞች በሶዶ ከተማ የሌማት ትሩፋትና በወጣቶች ስራ ዕድል ፈጠራ የተሰሩ የተለያዩ የልማት ስራዎችን ነው የጎበኙት።
ሠልጣኞች ከንድፈ ሀሳብ ባሻገር ልምድ ልውውጥ ማድረግ ፋይዳዉ ጉልህ ሚና እንዳለውም ተመላክቷል።
“የህልም ጉልበት ለእምርታዊ እድገት” በሚል ሀሳብ በወላይታ ዞን በየደረጃው የሚገኙ 1 ሺህ 5 መቶ የሚጠጉ አመራሮች በወላይታ ሶዶ ከተማ ስልጠናውን እየወሰዱ መሆናቸውን ይታወሳል።
ዘጋቢ ፡ በቀሌች ጌቾ -ከዋካ ቅርንጫፍ

More Stories
ከ23 ሚሊየን በላይ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች እንደሚተከሉ ተገለጸ
በግንቦት እና ሰኔ 2018 ዓ.ም ወራት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ፣ በቱሪዝም፣ በአረንጓዴ ዐሻራ፣ በዲጂታል ኢትዮጵያ፣ በሀገር በቀል ሪፎርም እና ቀጣናዊ ዲፕሎማሲ ዙሪያ ላይ ያተኮሩ የተለያዩ ከፍተኛ የሥራ ክንውኖችን አድርገዋል።
በህገወጥ መንገድ ከሀገር መውጣት ከህግ፣ ከደህንነት እና ከማህበራዊ አንፃር ከባድ ችግሮችን እንደሚያስከትል ተገለጸ