ከልብ ጋር የተያያዘ ህመም አጋጥሞት የነበረው የማንቸስተር ዩናይትዱ የመስመር ተከላካይ ኑሳይር ማዝራዊ ወደ ልምምድ መመለሱ ተገልጿል።
ሞሮኮአዊው ተጫዋች ባጋጠመው ህመም አነስተኛ የቀዶ ህክምና አድርጎ ነበር።
አሁን ላይ ግን ማዝራዊ ከህመሙ በማገገሙ ማንቸስተር ዩናይትድ በነገው ዕለት ከብሬንትፎርድ ጋር ከቀኑ 11 ሰዓት ለሚያከናውነው የፕሪሚዬር ሊግ ጨዋታ በስብስቡ እንደሚካተት አሰልጣኝ ኤሪክ ቴንሃግ አሳውቀዋል።
በሌላ በኩል የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል ወሳኝ ተጫዋቾቹ ቡካዮ ሳካ፣ ካይ ሃቨርትዝ እና ቶማስ ፓርቴ ለጨዋታ ዝግጁ መሆናቸው ተገልጿል።
የክለቡ አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ እንደገለፁት ሶስቱም ተጫዋቾች ከጉዳታቸው አገግመው በነገው ዕለት ከበርንማውዝ ጋር በሚካሄደው የሊጉ መርሐግብር መሰለፍ እንደሚችሉ ገልፀዋል።
ስፔናዊው አሰልጣኝ አያይዘውም የክለቡ አንበል ማርቲን ኦዴጋርድ በህዳር ወር ከሚካሄደው የሀገራት ጨዋታ አስቀድሞ ወደ ጨዋታ እንደሚመለስ አመላክተዋል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
ሀዋሳ ከተማ መቀሌ 70 እንደርታን አሸነፈ
ኦክስሌድ ቻምበርሌን በአርሰናል ልምምድ መስራት ጀመረ
ቱርክ 149 የእግር ኳስ ዳኞችን አገደች