የምስራቅ ጉራጌ ዞን አሰተዳደር በስልጤ ዞን በጎርፍ ለተጎዱ የህብረተሰብ ክፍሎች ለመጠለያ ግንባታ የሚሆን 1 ሚሊየን ብር የሚገመት ቁሳቁስ ድጋፍ ማድረጉ ተገለጸ
በዚሁ ወቅት የስልጤ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ሙበራ ከማል፤ በጎርፍ ምክንያት የተፈናቀሉ ወገኖች የኛም ወገኖች ናቸው፤ ጉዳታቸው ጉዳታችን ነው ብሎ ለቤት ግንባታ የሚያስፈልጉ ቁሳቁሶችን ድጋፍ ላደረገው የምስራቅ ጉራጌ ዞን አስተዳደር የላቀ ምስጋና አቅርበዋል።
የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙስጠፋ ሀሰን ድጋፉ በስልጤ ዞን በጎርፍ ለተጉዱ ወገኖች በአራት መኪና ለቤት ግንባታ የሚሆን ፍልጥ፣ ማገርና ተሸጋጋሪ የሚሆን ቁሳቁስ ነው ብለዋል።
ወንድማዊና ጎሮቤታዊ ፍቅራችንን ለመግለፅ ጅምር ድጋፍ ነው ያሉት አቶ ሙስጠፋ አብሮነታችንን በማጠናከርና ሰው ሰራሽም ይሆን የተፈጥሮ ችግሮች ሲያጋጥሙን በጋራ ለመካፈል ማሳያ ነው ብለዋል።
የምስራቅ ጉራጌ ዞን የጎረቤት ህዝብ ከተጎጂዎች ጎን በመሆን የሚያስፈልጉ ድጋፎችን ሁሉ በቀጣይም ያደርጋል ብለዋል።
ምንጭ፡ የስልጤ ዞን የመንግስት ኮሙኒኬሽን
More Stories
“አንድነታችንን በማጎልበት የህዝብ ጥቅም የሚያስቀድም ፖለቲካ ማራመድ ይጠበቅብናል” ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ
የሕብረ-ብሔራዊ አንድነት መጠናከር መሰረት የሆነው ብዝሃነትን በአግባቡ የማስተናገድ ሂደት ዘርፈ ብዙ ፋይዳ ያለው መሆኑ ተገለፀ
በክረምቱ ወራት ሊከሰቱ የሚችሉ የተለያዩ አደጋዎችን ለመከላከል አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ላይ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ገለጸ