ማህበረሰቡ የተፈጠረላቸውን ምቹ ሁኔታዎች በመጠቀም በግብርናው ዘርፍ የተሻለ ምርት ሊያመርቱ እንደሚገባ ተጠቆመ
ሀዋሳ፡ ጥቅምት 07/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የሌማት ትሩፋት እና የ30 40 30 እሳቤዎችን በመተግበር ውጤታማ መሆናቸዉን በደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ነዋሪዎች ተናገሩ።
በዘርፉ የሚስተዋሉ የአፈፃፀም ችግሮችን በመቅረፍ የአካባቢዉ ማህበረሰብና የተቋማት ተወካዮች የሚፈጠርላቸዉን ግንዛቤ ወደ መሬት ያወረዱ በመሆኑ ተጠቃሚ እየሆኑ ነዉ።
ወጣት ፈለቀ ፋኩ አርብቶ አደር ሜሪ ሙሌ፤ አባይነህ ሊራሶ እና ሌሎች እንደገለፁት በአትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም በንብ ማነብ ዘርፍ በተዘረጉ የልማት ፕሮጀክቶች በመሣተፍ ተጠቃሚ እየሆኑ ነዉ።
የወረዳዉ ግብርና ጽ/ቤት የሰብል ኤክስቴንሽን ዘርፍ እና የጽ/ቤቱ ምክትል ኃላፊ አቶ ጌትነት ከበደ፤ የአካባቢዉን ማህበረሰብ የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ እየተሠሩ ባሉ ስራዎች አበረታች ዉጤቶች እየተመዘገበ መሆኑን አመላክተዋል።
ሃላፊዉ አያይዘዉም በወረዳው የአካባቢዉ ማህበረሰብ የተፈጠረላቸውን ምቹ ሁኔታዎች ተጠቅመዉ ከዚህ በላይ አልምተው መጠቀም የሚችሉበት ሰፊ መሬትና በቂ የውሃ አማራጭ እንዳለ ጠቅሰዉ በተያዘው የምርት ዘመን በግብርናዉ ዘርፍ እንደ ወረዳ 5 ሺ 6 መቶ ሄክታር እየለማ እንዳለ ተናግረዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ወንድማገኝ በቀለ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
ህብር ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የምርጫ ማኒፌስቶ፣ የዕጩ ማስተዋወቂያ እንዲሁም የምርጫ ቅስቀሳ ፕሮግራም በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ አካሄደ
ኦርቢስ ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ ጥራት ያለው የአይን ህክምና በሀገሪቱ ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየሰራ መሆኑ ተገለፀ
ብልጽግና ፓርቲ የማህበረሰቡ ችግር የሚቀርፉ ፕሮጀክቶችን ገንብቶ በማጠናቀቅ በውጤታማነት ለአገልግሎት እያበቃ ነው – ዶ/ር መሀመድ ኑርዬ