ሀዋሳ፡ ጥቅምት 06/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በህዝቡ ዘንድ የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመቅረፍ ቅድሚያ ተሰጥቶት እንደሚሰራ የዳውሮ ዞን የስራ ሀላፊዎች ገለጹ፡፡
ሰሞኑን በጣለው ከባድ ዝናብ የዋካ ኢሠራ መንገድ ተበላሽቶ ለሳምንታት ያህል ዝግ ሊሆን መቻሉ ተመላክቷል።
ህብረተሰቡ ለማህበራዊና ኢኮኖሚያዊና ጫና መጋለጡን የጠቆሙት የዞኑ የሥራ ሃላፊዎች ይህንን ችግር ለመቅረፍ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እንደሚሰሩ ጠቁመው፥ ችግሩ በታየበት አካባቢ በአካል ተገኝተው የመንገድ ጥገናና ከፈታ ስራ ማስጀመራቸው ተመላክቷል፡፡
አስተያየታቸውን ከሰጡን የሥራ ሃላፊዎች መካከል አቶ ባቲሳ በተላ እና አቶ አንድነት ቡንጉዶ የህዝቡን የመልካም አስተዳደር ችግርና አንገብጋቢ ጉዳይ ለይቶ በመፍታትና ያጋጠመውን የመንገድ መሠረተ ልማት ችግር ለመቅረፍ ትኩረት አድርገው እየሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።
በዚህ የመንገድ ጥገና ስራ በዝናብ ወቅት ተበላሽቶ አገልግሎት ሳይሰጥ ለሳምንታት የቆየውን መንገድ ዳግም ስራ ማስጀመር ላይ ትኩረት መስጠታቸውን ገልጸዋል፡፡
የዳውሮ ምክትል አስተዳዳሪ አቶ አስፋው መሸሻ በበኩላቸው ብልፅግና ፓርቲ ለህዝቡ የገባውን የመልካም አስተዳደር ችግር መቅረፍ ዋነኛ የትኩረት አቅጣጫ መሆኑን አመላክተው፥ የዋካ ኢሠራ መንገድ ብልሽት ብዙ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ችግሮችን ያስከተለ በመሆኑ፥ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት ሰርቶ ለችግሩ እልባት ለመስጠት እንደሚሠራ ተናግረዋል።
ዘጋቢ፡ አፈወርቅ ኦሹ – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
የሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ በስፖርትና ባህል ልማት ዘርፍ የሚገኘውን ተጠቃሚነት ለማሳደግ አበክሮ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
ህግና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን ፍትህ ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት ሥራ አፈፃፀም አደመጠ
ከተማዋን ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ እንደሚሠራ የዲላ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ