ባህር ዛፍ በባህሪው ከረጅም ጊዜ በኋላ ለአገልግሎት የሚደርስና የመሬት ለምነትንም የሚያጠፋ በመሆኑ ከእርሻ ማሳቸው እያስወገዱ እንደሚገኙ ተናግረዋል ።
የወረዳው አርሶአደሮች በአጭር ጊዜ ምርት ከሚሰጡ የጓሮ አትክልቶችና ሰብሎች የሚያገኙትን ጥቅም በማነፃፀር አስረድተዋል፡፡
የደቡብ ኣሪ ወረዳ ግብርና ልማት ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ዮሐንስ ማምሶ በበኩላቸው የወረዳው አርሶአደሮች በራሳቸው ተነሳሽነት ከማሳቸው የባህርዛፍ ተክልን በማስወገድ በተለያዩ የጓሮ አትክልትና ሰብሎች እየሸፈኑ እንደሚገኙ ገልፀዋል።
ሀላፊው አያይዘውም የባህር ዛፍ ተክል ለተለያዩ አገልግሎቶች ጠቃሚ በመሆኑ ለተክሉ አመቺ በሆኑና በተመረጡ ስፍራዎች ማልማት እንደሚቻል አስረድተዋል።
ዘጋቢ፡ ዳኜ ጥላሁን – ከጂንካ ጣቢያችን
More Stories
አሁን ላይ እየተባባሰ የመጣውን የወባ በሽታ ስርጭት ለመቆጣጠር በተቀናጀ ሁኔታ እየተሠራ ነው – በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የጠምባሮ ልዩ ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት
በጌዴኦ ዞን ዲላ ከተማ ከ18 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባው የዳራሮ ሁለተኛ ደረጃ የሽግግር አዳሪ ትምህርት ቤት ተመረቀ
በኮቾሬ ወረዳ በተለያዩ ምክንያቶች በመበላሸት ለረጅም ዓመታት የተቋረጡ የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ተጠግነው ለሕብረተሰቡ ግልጋሎት ክፍት ሆነዋል