ባህር ዛፍ በባህሪው ከረጅም ጊዜ በኋላ ለአገልግሎት የሚደርስና የመሬት ለምነትንም የሚያጠፋ በመሆኑ ከእርሻ ማሳቸው እያስወገዱ እንደሚገኙ ተናግረዋል ።
የወረዳው አርሶአደሮች በአጭር ጊዜ ምርት ከሚሰጡ የጓሮ አትክልቶችና ሰብሎች የሚያገኙትን ጥቅም በማነፃፀር አስረድተዋል፡፡
የደቡብ ኣሪ ወረዳ ግብርና ልማት ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ዮሐንስ ማምሶ በበኩላቸው የወረዳው አርሶአደሮች በራሳቸው ተነሳሽነት ከማሳቸው የባህርዛፍ ተክልን በማስወገድ በተለያዩ የጓሮ አትክልትና ሰብሎች እየሸፈኑ እንደሚገኙ ገልፀዋል።
ሀላፊው አያይዘውም የባህር ዛፍ ተክል ለተለያዩ አገልግሎቶች ጠቃሚ በመሆኑ ለተክሉ አመቺ በሆኑና በተመረጡ ስፍራዎች ማልማት እንደሚቻል አስረድተዋል።
ዘጋቢ፡ ዳኜ ጥላሁን – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
በጎፋ ዞን የዑባ ደብረፀሐይ ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ፓርቲውን በሀብት ለማጠናከር ከ1 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር በላይ የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ
የጓሮ አትክልትና የተለያዩ ሰብሎችን በማልማት የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ መቻላቸውን በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የሶያሜ ቀበሌ አርሶአደሮች ተናገሩ
በከተማው በተያዘው በጀት ዓመት በ5 ወራት ውስጥ 1 ቢሊየን 5 ሚሊዮን ብር ገቢ መሰብሰብ መቻሉን የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ አስታወቀ