ባህር ዛፍ በባህሪው ከረጅም ጊዜ በኋላ ለአገልግሎት የሚደርስና የመሬት ለምነትንም የሚያጠፋ በመሆኑ ከእርሻ ማሳቸው እያስወገዱ እንደሚገኙ ተናግረዋል ።
የወረዳው አርሶአደሮች በአጭር ጊዜ ምርት ከሚሰጡ የጓሮ አትክልቶችና ሰብሎች የሚያገኙትን ጥቅም በማነፃፀር አስረድተዋል፡፡
የደቡብ ኣሪ ወረዳ ግብርና ልማት ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ዮሐንስ ማምሶ በበኩላቸው የወረዳው አርሶአደሮች በራሳቸው ተነሳሽነት ከማሳቸው የባህርዛፍ ተክልን በማስወገድ በተለያዩ የጓሮ አትክልትና ሰብሎች እየሸፈኑ እንደሚገኙ ገልፀዋል።
ሀላፊው አያይዘውም የባህር ዛፍ ተክል ለተለያዩ አገልግሎቶች ጠቃሚ በመሆኑ ለተክሉ አመቺ በሆኑና በተመረጡ ስፍራዎች ማልማት እንደሚቻል አስረድተዋል።
ዘጋቢ፡ ዳኜ ጥላሁን – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በክልሉ ለሚገኙ የዘርፉ ባለሙያዎች ስልጠና መስጠት ጀመረ
የቅድመ በሽታ መከላከል ተግባራትን በአግባቡ በመፈፀም ጤናማ ትውልድ ለመፍጠር በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የሸዋል ዒድ (ቀሊ ፍቼ) ባህላዊ ስርዓት በስልጤ