ባህር ዛፍ በባህሪው ከረጅም ጊዜ በኋላ ለአገልግሎት የሚደርስና የመሬት ለምነትንም የሚያጠፋ በመሆኑ ከእርሻ ማሳቸው እያስወገዱ እንደሚገኙ ተናግረዋል ።
የወረዳው አርሶአደሮች በአጭር ጊዜ ምርት ከሚሰጡ የጓሮ አትክልቶችና ሰብሎች የሚያገኙትን ጥቅም በማነፃፀር አስረድተዋል፡፡
የደቡብ ኣሪ ወረዳ ግብርና ልማት ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ዮሐንስ ማምሶ በበኩላቸው የወረዳው አርሶአደሮች በራሳቸው ተነሳሽነት ከማሳቸው የባህርዛፍ ተክልን በማስወገድ በተለያዩ የጓሮ አትክልትና ሰብሎች እየሸፈኑ እንደሚገኙ ገልፀዋል።
ሀላፊው አያይዘውም የባህር ዛፍ ተክል ለተለያዩ አገልግሎቶች ጠቃሚ በመሆኑ ለተክሉ አመቺ በሆኑና በተመረጡ ስፍራዎች ማልማት እንደሚቻል አስረድተዋል።
ዘጋቢ፡ ዳኜ ጥላሁን – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
ህብር ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የምርጫ ማኒፌስቶ፣ የዕጩ ማስተዋወቂያ እንዲሁም የምርጫ ቅስቀሳ ፕሮግራም በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ አካሄደ
ኦርቢስ ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ ጥራት ያለው የአይን ህክምና በሀገሪቱ ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየሰራ መሆኑ ተገለፀ
ብልጽግና ፓርቲ የማህበረሰቡ ችግር የሚቀርፉ ፕሮጀክቶችን ገንብቶ በማጠናቀቅ በውጤታማነት ለአገልግሎት እያበቃ ነው – ዶ/ር መሀመድ ኑርዬ