የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ለመማር ማስተማር አገልግሎት እና ለዘመናዊ እንስሳት እርባታ አገልግሎት የሚውል የመኖ ማቀነባበሪያ ማሽኖች ግዥ መፈፀሙን አስታውቋል፡፡
የጂንካ ዩኒቨርሲቲ የእንስሳት ስነ-ምግብ መምህር እና ተመራማሪ አቶ አምባ ጩፋ እንደገለፁት፤ ዩኒቨርሲቲው የገዛቸው ዘመናዊ የመኖ ማቀነባበሪያ ማሽኖች ተማሪዎች የሚማሩት ትምህርት በተግባር የተደገፈ እንዲሆን የሚያስችሉ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
የዩኒቨርሲቲው መምህርና የግብርና ኮሌጁ ዲን አቶ ግርማ ዳዊት በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲው የእንስሳት መኖ ማቀነባበሪያ ማሽኖችን በ30 ሚሊዮን ብር መግዛቱን ገልፀዋል፡፡
ማሽኖቹ ተማሪዎች በተግባር ትምህርታቸውን እንዲማሩ ከማስቻላቸውም በተጨማሪ በግቢ ውስጥ ላሉ የተሻሻሉ የወተት ላሞችና የቦረና ጊደሮች እንዲሁም በቀጣይ ዩኒቨርሲቲው ላቀደው የዓሳ እርባታ ስራ መኖ እያቀነባበሩ እንደሚያቀርቡ ገልፀዋል፡፡
የኮሌጁ ዲን፤ ከዚህ በፊት ዩኒቨርሲቲው ለተሻሻሉ የወተት ላሞች አንድ ኩንታል የተቀነባበረ መኖ ለመግዛት የሚያወጣውን አምስት ሺ ብር እንደሚያስቀርና ማቀነባበሪያ ማሽኖቹ ለዘመናዊ የእንስሳት እርባታ ጉልህ ሚና እንዳላቸውም ተናግረዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ወሰኑ ዶይዴ – ከጂንካ ጣቢያችን
More Stories
“አንድነታችንን በማጎልበት የህዝብ ጥቅም የሚያስቀድም ፖለቲካ ማራመድ ይጠበቅብናል” ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ
የሕብረ-ብሔራዊ አንድነት መጠናከር መሰረት የሆነው ብዝሃነትን በአግባቡ የማስተናገድ ሂደት ዘርፈ ብዙ ፋይዳ ያለው መሆኑ ተገለፀ
በክረምቱ ወራት ሊከሰቱ የሚችሉ የተለያዩ አደጋዎችን ለመከላከል አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ላይ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ገለጸ