የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ለመማር ማስተማር አገልግሎት እና ለዘመናዊ እንስሳት እርባታ አገልግሎት የሚውል የመኖ ማቀነባበሪያ ማሽኖች ግዥ መፈፀሙን አስታውቋል፡፡
የጂንካ ዩኒቨርሲቲ የእንስሳት ስነ-ምግብ መምህር እና ተመራማሪ አቶ አምባ ጩፋ እንደገለፁት፤ ዩኒቨርሲቲው የገዛቸው ዘመናዊ የመኖ ማቀነባበሪያ ማሽኖች ተማሪዎች የሚማሩት ትምህርት በተግባር የተደገፈ እንዲሆን የሚያስችሉ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
የዩኒቨርሲቲው መምህርና የግብርና ኮሌጁ ዲን አቶ ግርማ ዳዊት በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲው የእንስሳት መኖ ማቀነባበሪያ ማሽኖችን በ30 ሚሊዮን ብር መግዛቱን ገልፀዋል፡፡
ማሽኖቹ ተማሪዎች በተግባር ትምህርታቸውን እንዲማሩ ከማስቻላቸውም በተጨማሪ በግቢ ውስጥ ላሉ የተሻሻሉ የወተት ላሞችና የቦረና ጊደሮች እንዲሁም በቀጣይ ዩኒቨርሲቲው ላቀደው የዓሳ እርባታ ስራ መኖ እያቀነባበሩ እንደሚያቀርቡ ገልፀዋል፡፡
የኮሌጁ ዲን፤ ከዚህ በፊት ዩኒቨርሲቲው ለተሻሻሉ የወተት ላሞች አንድ ኩንታል የተቀነባበረ መኖ ለመግዛት የሚያወጣውን አምስት ሺ ብር እንደሚያስቀርና ማቀነባበሪያ ማሽኖቹ ለዘመናዊ የእንስሳት እርባታ ጉልህ ሚና እንዳላቸውም ተናግረዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ወሰኑ ዶይዴ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
ሀገራዊ ምክክር፤ የመደማመጥ፣ የመግባባትና የጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ መሠረት ነው!
ከ23 ሚሊየን በላይ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች እንደሚተከሉ ተገለጸ
በግንቦት እና ሰኔ 2018 ዓ.ም ወራት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ፣ በቱሪዝም፣ በአረንጓዴ ዐሻራ፣ በዲጂታል ኢትዮጵያ፣ በሀገር በቀል ሪፎርም እና ቀጣናዊ ዲፕሎማሲ ዙሪያ ላይ ያተኮሩ የተለያዩ ከፍተኛ የሥራ ክንውኖችን አድርገዋል።