የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ለመማር ማስተማር አገልግሎት እና ለዘመናዊ እንስሳት እርባታ አገልግሎት የሚውል የመኖ ማቀነባበሪያ ማሽኖች ግዥ መፈፀሙን አስታውቋል፡፡
የጂንካ ዩኒቨርሲቲ የእንስሳት ስነ-ምግብ መምህር እና ተመራማሪ አቶ አምባ ጩፋ እንደገለፁት፤ ዩኒቨርሲቲው የገዛቸው ዘመናዊ የመኖ ማቀነባበሪያ ማሽኖች ተማሪዎች የሚማሩት ትምህርት በተግባር የተደገፈ እንዲሆን የሚያስችሉ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
የዩኒቨርሲቲው መምህርና የግብርና ኮሌጁ ዲን አቶ ግርማ ዳዊት በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲው የእንስሳት መኖ ማቀነባበሪያ ማሽኖችን በ30 ሚሊዮን ብር መግዛቱን ገልፀዋል፡፡
ማሽኖቹ ተማሪዎች በተግባር ትምህርታቸውን እንዲማሩ ከማስቻላቸውም በተጨማሪ በግቢ ውስጥ ላሉ የተሻሻሉ የወተት ላሞችና የቦረና ጊደሮች እንዲሁም በቀጣይ ዩኒቨርሲቲው ላቀደው የዓሳ እርባታ ስራ መኖ እያቀነባበሩ እንደሚያቀርቡ ገልፀዋል፡፡
የኮሌጁ ዲን፤ ከዚህ በፊት ዩኒቨርሲቲው ለተሻሻሉ የወተት ላሞች አንድ ኩንታል የተቀነባበረ መኖ ለመግዛት የሚያወጣውን አምስት ሺ ብር እንደሚያስቀርና ማቀነባበሪያ ማሽኖቹ ለዘመናዊ የእንስሳት እርባታ ጉልህ ሚና እንዳላቸውም ተናግረዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ወሰኑ ዶይዴ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
ህብር ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የምርጫ ማኒፌስቶ፣ የዕጩ ማስተዋወቂያ እንዲሁም የምርጫ ቅስቀሳ ፕሮግራም በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ አካሄደ
ኦርቢስ ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ ጥራት ያለው የአይን ህክምና በሀገሪቱ ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየሰራ መሆኑ ተገለፀ
ብልጽግና ፓርቲ የማህበረሰቡ ችግር የሚቀርፉ ፕሮጀክቶችን ገንብቶ በማጠናቀቅ በውጤታማነት ለአገልግሎት እያበቃ ነው – ዶ/ር መሀመድ ኑርዬ