ሀዋሳ፡ መስከረም 25/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመጀመሪያው የትምህርት ሴክተር ጉባኤ እየተካሄደ ይገኛል።
ክልልሉ ከተመሰረተ በኃላ የመጀመሪያውን የትምህርት ጉባኤ “የላቀ ትጋት ለትምህርት ጥራት” በሚል መሪ ቃል ነው በማረቆ ልዩ ወረዳ ቆሼ ከተማ እየተካሄደ ያለው።
በዕለቱም የክልሉ ትምህርት ቢሮ የ2016 ዓ.ም ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት እንዲሁም የ2017 ዕቅድ ይቀርባል።
በዕለቱ የቅድመ አንደኛ ትምህርትና የትምህርት ቤት ምገባ ፕሮግራሞች ዕቅድ ቀርቦ ይመከርበታል።
የክልሉ መምህራን ማህበር ሪፖርት የ2016 ዓ.ም ክልላዊና አገር አቀፋዊ የፈተና ውጤትና ተያያዥ ጉዳዮች በሴክቶሪያል ጉባኤው ውይይት ይደረግባቸዋል።
በመድረኩም የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው ም/ርዕሰ መስተዳድር የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ሀላፊው አንተነህ ፈቃዱ እንዲሁም ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ታድመዋል፡፡
ዘጋቢ: ባዬ በልስቲ
More Stories
ዲጂታል ኢትዮጵያን የመፍጠሪያ ጊዜን በማፋጠን ኢትዮጵያን የመጪው ዘመን መሪ ለማድረግ በትኩረት መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
የሆሳዕና እናት ቃለ ህይወት ቤተክርስቲያን አዲሱን ዓመት ምክንያት በማድረግ ከአንድ መቶ በላይ ለሚሆኑ አቅመ ደካሞች የምግብ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገች
እመርታ ለዘላቂ ከፍታ!