ሀዋሳ፡ መስከረም 25/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመጀመሪያው የትምህርት ሴክተር ጉባኤ እየተካሄደ ይገኛል።
ክልልሉ ከተመሰረተ በኃላ የመጀመሪያውን የትምህርት ጉባኤ “የላቀ ትጋት ለትምህርት ጥራት” በሚል መሪ ቃል ነው በማረቆ ልዩ ወረዳ ቆሼ ከተማ እየተካሄደ ያለው።
በዕለቱም የክልሉ ትምህርት ቢሮ የ2016 ዓ.ም ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት እንዲሁም የ2017 ዕቅድ ይቀርባል።
በዕለቱ የቅድመ አንደኛ ትምህርትና የትምህርት ቤት ምገባ ፕሮግራሞች ዕቅድ ቀርቦ ይመከርበታል።
የክልሉ መምህራን ማህበር ሪፖርት የ2016 ዓ.ም ክልላዊና አገር አቀፋዊ የፈተና ውጤትና ተያያዥ ጉዳዮች በሴክቶሪያል ጉባኤው ውይይት ይደረግባቸዋል።
በመድረኩም የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው ም/ርዕሰ መስተዳድር የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ሀላፊው አንተነህ ፈቃዱ እንዲሁም ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ታድመዋል፡፡
ዘጋቢ: ባዬ በልስቲ

More Stories
በጎፋ ዞን የዑባ ደብረፀሐይ ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ፓርቲውን በሀብት ለማጠናከር ከ1 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር በላይ የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ
የጓሮ አትክልትና የተለያዩ ሰብሎችን በማልማት የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ መቻላቸውን በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የሶያሜ ቀበሌ አርሶአደሮች ተናገሩ
በከተማው በተያዘው በጀት ዓመት በ5 ወራት ውስጥ 1 ቢሊየን 5 ሚሊዮን ብር ገቢ መሰብሰብ መቻሉን የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ አስታወቀ