ሀዋሳ፡ መስከረም 25/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመጀመሪያው የትምህርት ሴክተር ጉባኤ እየተካሄደ ይገኛል።
ክልልሉ ከተመሰረተ በኃላ የመጀመሪያውን የትምህርት ጉባኤ “የላቀ ትጋት ለትምህርት ጥራት” በሚል መሪ ቃል ነው በማረቆ ልዩ ወረዳ ቆሼ ከተማ እየተካሄደ ያለው።
በዕለቱም የክልሉ ትምህርት ቢሮ የ2016 ዓ.ም ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት እንዲሁም የ2017 ዕቅድ ይቀርባል።
በዕለቱ የቅድመ አንደኛ ትምህርትና የትምህርት ቤት ምገባ ፕሮግራሞች ዕቅድ ቀርቦ ይመከርበታል።
የክልሉ መምህራን ማህበር ሪፖርት የ2016 ዓ.ም ክልላዊና አገር አቀፋዊ የፈተና ውጤትና ተያያዥ ጉዳዮች በሴክቶሪያል ጉባኤው ውይይት ይደረግባቸዋል።
በመድረኩም የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው ም/ርዕሰ መስተዳድር የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ሀላፊው አንተነህ ፈቃዱ እንዲሁም ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ታድመዋል፡፡
ዘጋቢ: ባዬ በልስቲ
More Stories
ጥራት ያለው የጤና አገልግሎትን ለማህበረሰቡ ተደራሽ ለማድረግ የጤና ባለሙያዎች በኃላፊነት ሊሰሩ እንደሚገባ በጌዴኦ ዞን የይርጋጨፌ ወረዳ አስተዳደር አስታወቀ
የባስኬቶ ዞን ተወላጆች የአንድነት መድረክ ማጠቃለያ እየተካሄደ ነው
በእንስሳት እርባታ ከተሰማራን ወዲህ ኑሯችን ተሻሽሏል – የጋዘር ከተማ ወጣቶች