ሀዋሳ፡ መስከረም 25/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመጀመሪያው የትምህርት ሴክተር ጉባኤ እየተካሄደ ይገኛል።
ክልልሉ ከተመሰረተ በኃላ የመጀመሪያውን የትምህርት ጉባኤ “የላቀ ትጋት ለትምህርት ጥራት” በሚል መሪ ቃል ነው በማረቆ ልዩ ወረዳ ቆሼ ከተማ እየተካሄደ ያለው።
በዕለቱም የክልሉ ትምህርት ቢሮ የ2016 ዓ.ም ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት እንዲሁም የ2017 ዕቅድ ይቀርባል።
በዕለቱ የቅድመ አንደኛ ትምህርትና የትምህርት ቤት ምገባ ፕሮግራሞች ዕቅድ ቀርቦ ይመከርበታል።
የክልሉ መምህራን ማህበር ሪፖርት የ2016 ዓ.ም ክልላዊና አገር አቀፋዊ የፈተና ውጤትና ተያያዥ ጉዳዮች በሴክቶሪያል ጉባኤው ውይይት ይደረግባቸዋል።
በመድረኩም የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው ም/ርዕሰ መስተዳድር የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ሀላፊው አንተነህ ፈቃዱ እንዲሁም ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ታድመዋል፡፡
ዘጋቢ: ባዬ በልስቲ

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በክልሉ ለሚገኙ የዘርፉ ባለሙያዎች ስልጠና መስጠት ጀመረ
የቅድመ በሽታ መከላከል ተግባራትን በአግባቡ በመፈፀም ጤናማ ትውልድ ለመፍጠር በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የሸዋል ዒድ (ቀሊ ፍቼ) ባህላዊ ስርዓት በስልጤ