ሀዋሳ፡ መስከረም 24/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የኢፌዲሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት የ2016 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ እና የ2017 ዕቅድ ትውውቅ መድረክ “ዓመተ ልህቀት 2” በሚል መሪ ቃል በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።
የኢፌዲሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ብሩክ ከድር በመክፈቻ ንግግራቸው ወቅት እንደገለፁት ልህቀት በአንድ ጊዜ ስለማይመጣ ሀገሪቱን በቴክኖሎጂ ለማዘመን በቅንጅት ይሰራል ብለዋል።
አምና አንድ ብለን ጀምረን አሁን ዓመተ ልህቀት ሁለት ላይ ደርሰናል ያሉት ዳይሬክተሩ፤ ለላቀ የሀገር ለውጥ ዘርፉን በማሳደግ ካደጉት ሀገሮች ተርታ ለመሰለፍ እንደሚሰራ አመላክተዋል።
መድረኩ ለሁለት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ሲሆን የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ብሩክ ከድርን ጨምሮ የኢንስቲትዩቱ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች እየተሳተፉ ይገኛል።
ዘጋቢ: አማኑኤል አጤቦ – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
የሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ በስፖርትና ባህል ልማት ዘርፍ የሚገኘውን ተጠቃሚነት ለማሳደግ አበክሮ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
ህግና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን ፍትህ ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት ሥራ አፈፃፀም አደመጠ
ከተማዋን ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ እንደሚሠራ የዲላ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ