መምሪያው “የግብዓት አቅርቦት ለትምህርት ስኬት ቀን” በሚል ቀኑን በማስመልከት በዞኑና በክልሉ ድጋፍ የተዘጋጀውን የተማሪዎች መጻህፍት ማሰራጨቱን አስታውቋል፡፡
በዚሁ ወቅት የጌዴኦ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ዘማች ክፍሌ በትምህርት ሳምንት የግብዓት ቀንን በማስመልከት በሁሉም ትምህርት ቤቶች የመጽሐፍት ሥርጭት በስፋት እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የመጽሀፍት አቅርቦት ለተማሪዎች ውጤት ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው የገለጹት አቶ ዘማች፤ የግብዓት አቅርቦት ችግሮችን ለመፍታት አንድ መጽሐፍ ለአንድ ተማሪ በሚል ንቅናቄ በርካታ የህብረተሰብ ክፍሎች ርብርብ ማድረጋቸውን አስረድተዋል፡፡
በትምህርት ሚኒስቴር፣ በክልል ትምህርት ቢሮና በአንድ መጽሐፍ ለአንድ ተማሪ ዘመቻ በተሰበሰበ ሀብት የታተመው ከ197 ሺህ በላይ የመማሪያ መጻሕፍት መሰራጨታቸውን የገለጹት ኃላፊው በ2015 እና 2016 ዓ.ም ተሰራጭተው በትምህርት ቤቶች ያሉ መጻሐፍት ለተማሪዎች መከፋፈላቸውን አብራርተዋል፡፡
መጻሕፍቱ ከፍተኛ የመንግሥትና የህዝብ ገንዘብ ፈሶባቸው የታተሙ በመሆናቸው ሳይበላሹ ለትውልድ እንዲቆዩ በጥንቃቄ ለመያዝ ሁሉም ባለድርሻዎች የበኩላቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል፡፡
ዘጋቢ፡ እምነት ሸፈራው – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
በኮሪደር ልማት፣ የመንገድ ግንባታ እና ተያያዥ ስራዎች በፍጥነት እንዲጠናቀቁ የጠቅላላ ተቋራጮች እና የአገልግሎት ተቋማት ትጋትና ቁርጠኝነት የሚበረታታ መሆኑ ተገለጸ
በሴቶች ላይ የሚደርሱ ማህበራዊ ጫናዎችን ለመከላከል የኢኮኖሚ ባለቤት እንዲሆኑ ለማስቻል ሁሉም ባለድርሻ አካላላት ትኩረት ሊሰጡ እንደሚገባ ተገለፀ
ትምህርት ቤቶች የዉስጥ ገቢያቸዉን በማሳደግ የግብዓት ችግሮችን በመቅረፍ ምቹ የመማር ማስተማር ከባቢን መፍጠር እንዳለባቸዉ ተገለፀ