መምሪያው “የግብዓት አቅርቦት ለትምህርት ስኬት ቀን” በሚል ቀኑን በማስመልከት በዞኑና በክልሉ ድጋፍ የተዘጋጀውን የተማሪዎች መጻህፍት ማሰራጨቱን አስታውቋል፡፡
በዚሁ ወቅት የጌዴኦ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ዘማች ክፍሌ በትምህርት ሳምንት የግብዓት ቀንን በማስመልከት በሁሉም ትምህርት ቤቶች የመጽሐፍት ሥርጭት በስፋት እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የመጽሀፍት አቅርቦት ለተማሪዎች ውጤት ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው የገለጹት አቶ ዘማች፤ የግብዓት አቅርቦት ችግሮችን ለመፍታት አንድ መጽሐፍ ለአንድ ተማሪ በሚል ንቅናቄ በርካታ የህብረተሰብ ክፍሎች ርብርብ ማድረጋቸውን አስረድተዋል፡፡
በትምህርት ሚኒስቴር፣ በክልል ትምህርት ቢሮና በአንድ መጽሐፍ ለአንድ ተማሪ ዘመቻ በተሰበሰበ ሀብት የታተመው ከ197 ሺህ በላይ የመማሪያ መጻሕፍት መሰራጨታቸውን የገለጹት ኃላፊው በ2015 እና 2016 ዓ.ም ተሰራጭተው በትምህርት ቤቶች ያሉ መጻሐፍት ለተማሪዎች መከፋፈላቸውን አብራርተዋል፡፡
መጻሕፍቱ ከፍተኛ የመንግሥትና የህዝብ ገንዘብ ፈሶባቸው የታተሙ በመሆናቸው ሳይበላሹ ለትውልድ እንዲቆዩ በጥንቃቄ ለመያዝ ሁሉም ባለድርሻዎች የበኩላቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል፡፡
ዘጋቢ፡ እምነት ሸፈራው – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
More Stories
“አንድነታችንን በማጎልበት የህዝብ ጥቅም የሚያስቀድም ፖለቲካ ማራመድ ይጠበቅብናል” ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ
የሕብረ-ብሔራዊ አንድነት መጠናከር መሰረት የሆነው ብዝሃነትን በአግባቡ የማስተናገድ ሂደት ዘርፈ ብዙ ፋይዳ ያለው መሆኑ ተገለፀ
በክረምቱ ወራት ሊከሰቱ የሚችሉ የተለያዩ አደጋዎችን ለመከላከል አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ላይ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ገለጸ