መምሪያው “የግብዓት አቅርቦት ለትምህርት ስኬት ቀን” በሚል ቀኑን በማስመልከት በዞኑና በክልሉ ድጋፍ የተዘጋጀውን የተማሪዎች መጻህፍት ማሰራጨቱን አስታውቋል፡፡
በዚሁ ወቅት የጌዴኦ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ዘማች ክፍሌ በትምህርት ሳምንት የግብዓት ቀንን በማስመልከት በሁሉም ትምህርት ቤቶች የመጽሐፍት ሥርጭት በስፋት እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የመጽሀፍት አቅርቦት ለተማሪዎች ውጤት ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው የገለጹት አቶ ዘማች፤ የግብዓት አቅርቦት ችግሮችን ለመፍታት አንድ መጽሐፍ ለአንድ ተማሪ በሚል ንቅናቄ በርካታ የህብረተሰብ ክፍሎች ርብርብ ማድረጋቸውን አስረድተዋል፡፡
በትምህርት ሚኒስቴር፣ በክልል ትምህርት ቢሮና በአንድ መጽሐፍ ለአንድ ተማሪ ዘመቻ በተሰበሰበ ሀብት የታተመው ከ197 ሺህ በላይ የመማሪያ መጻሕፍት መሰራጨታቸውን የገለጹት ኃላፊው በ2015 እና 2016 ዓ.ም ተሰራጭተው በትምህርት ቤቶች ያሉ መጻሐፍት ለተማሪዎች መከፋፈላቸውን አብራርተዋል፡፡
መጻሕፍቱ ከፍተኛ የመንግሥትና የህዝብ ገንዘብ ፈሶባቸው የታተሙ በመሆናቸው ሳይበላሹ ለትውልድ እንዲቆዩ በጥንቃቄ ለመያዝ ሁሉም ባለድርሻዎች የበኩላቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል፡፡
ዘጋቢ፡ እምነት ሸፈራው – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
ከመማር ማስተማር ተግባር ባለፈ የአካባቢ ማህበረሰብ ተጠቃሚነት ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን የሚዛን ግብርና ቴክኒክ ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጅ አስታወቀ
የኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ(ዶ/ር) መጭው ጊዜ ከተስፋ ብርሃን ወደሚጨበጥ ብርሃን የምንሸጋገርበት ብሩህ ዘመን መሆኑን ተናገሩ
በተቀሩት አጭር ቀናት ህብረተሠቡ የመራጭነት ካርዱን በመውሰድ የዜግነት ግዴታውን እንዲወጣ የጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ወረዳና አካባቢው የፌደራልና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ጥሪ አቀረቡ