በዞኑ የአረም ቁጥጥር ሥራም እየተሠራ መሆኑ ተገልጿል።
በኮሬ ዞን ከ65 ሺህ ሄክታር በላይ ማሳ በሰብል የተሸፈነ ሲሆን ለጤፍ ምርት ሰፊ ሽፋን መሰጠቱ ተመላክቷል።
በዞኑ በ2017 የምርት ዘመን የመኸር እርሻ በኩታገጠም የታረሰው ሰብል ጥሩ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ የኮሬ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ፣ የግብርና መምሪያ ኃላፊና የኢኮኖሚ ክላስተር አስተባባሪ አቶ አስታረቀኝ አንደባ አስታውቀዋል።
የመካናይዜሽን ሥራ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱን የገለፁት አቶ አስታረቀኝ፤ ከ20 ሺህ በላይ ሄክታር መሬት በኩታገጠም መታረሱን እንዲሁም የተባይ ቁጥጥርና የአረም ተግባርም በትኩረት እየተሠራ ነው ብለዋል።
አክለውም አርሶ አደሮች በጊዜው አረምን እንዲቆጣጠሩና በማሳቸው ውስጥ እርጥበትን የሚያቆዩበትን ዘዴ እንዲጠቀሙ ጠቁመዋል።
ከዞኑ ካነጋገርናቸው መካከል ሞዴል አርሶአደር ኤልያስ ይልማ ወቅቱን ጠብቀው በትራክተር ወደ 3 ሄክታር አሳርሰው የዘሩት ጤፍ ጥሩ ደረጃ ላይ እንደሚገኝና የጉልበት ሠራተኞችን በማስተባበር አረምን የመቆጣጠር ተግባር እያከናወኑ እንደሚገኙ ነው የተናገሩት።
አርሶ አደር ኮምፓስ አለኬ የአቶ ኤልያስ ጎረቤት ሲሆኑ ከዚህ በፊት በበሬ ሲያርሱ ወቅቱን ከመጠበቅና ምርትን ከማሳደግ አንፃር ብዙም ተጠቃሚ እንዳልነበሩ በመግለጽ በጎረቤታቸው ተሞክሮ በትራክተር በስፋት አርሰው በማረም የተሻለ ምርት አንደሚጠብቁ ተናግረዋል።
ዘጋቢ፡ ምርጫ መላኩ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
ህዝበ ሙስሊሙ የመውሊድ በዓልን ሲያከብር በብዝሃነት ውስጥ የሚንፀባረቁ የመረዳዳትና የአብሮነት በጎ እሴቶችን ይበልጥ በማጠናከር ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ኃላፊና የየዞን ከፍተኛ አመራሮች በሣውላ ማረሚያ ተቋም አረንጓዴ አሻራቸውን በማኖር ልዩ ልዩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ
በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር ምርመራ እና ልየታ ተካሄደ