ሀዋሳ፡ መስከረም 21/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) 12ኛው የኢትዮጵያ ህብረ-ህዋስ ባንኮች ዓመታዊ ጉባኤ “ዘላቂ ፋይናንስ ለጠንካራ የደም እና ህብረ-ህዋስ አገልግሎት” በሚል መሪ ቃል በአርባምንጭ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።
ባለፉት በርካታ ዓመታት የህብረ-ህዋስ አገልግሎት የቆመለትን እና ህይወት የመታደግ አላማን ለማሳካት በርካታ ተግባራትን እያከናወነ መቆየቱ ተመላክቷል።
በመድረኩ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ም/ኃላፊ አቶ ናፍቆት ብርሀኑ እንዳሉት፤ በክልሉ የደምና የህብረ-ህዋስ አገልግሎትን ለማሻሻልና የደም ለጋሾችን ቁጥር ለማሳደግ ተጨባጭ ተግባራት ተከናውነዋል።
በቀጣይም የአገልግሎት አሰጣጡን ለማዘመን የፋይናንስ ችግርን መፍታት እንደሚያሻ ኃላፊው ጠቁመዋል።
የኢትዮጵያ ህብረ-ህዋስ ደም ባንክ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አሸናፊ ታዘበው በበኩላቸው አገልግሎቱ በ2016 በጀት ዓመት ከዕቅድና ከፍላጎት አንፃር የተሻለ አፈፃፀም ማስመዝገብ መቻሉን ተናግረዋል።
በተያዘው በጀት ዓመትም አገልግሎቱን ከማዘመንና ጥራትን ከማሳደግ አንፃር የሚስተዋለውን የፋይናንስ ችግር ለመፍታት ትኩረት እንደሚደረግ ጠቁመው ጥራትና ተደራሽነትን ለማሳደግ እንደሚሰራ ገልጸዋል ዶ/ር አሸናፊ።
የአገልግሎቱን የ2016 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀምን በተመለከተ ረፖርት ለመድረኩ ቀርቧል።
በመድረኩ በ2016 የላቀ አፈፃፀም ያስመዘገቡ የደም ባንክ አገልግሎቶች የማበረታቻ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
ዘጋቢ፡ ተመኙህ ገረሱ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን
More Stories
ፈጣንና ቀልጣፋ መረጃን ተጀራሽ በማድረግ የመንግስትና የማህበረሰቡን ተግባቦት ይበልጥ ለማጠናከር የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ሚና የጎላ መሆኑ ተጠቆመ
ሀገር አቀፍ የጥናትና ምርምር ኮንፍረንስ በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ እየተካሄደ ነው
በ17 ነጥብ 5 ሄክታር መሬት ላይ የሞሪንጋ ጂን ባንክ ለማቋቋም ታቅዶ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ