የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቡቶ አኒቶ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ሞገስ ባልቻ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ረዳት የመንግስት ተጠሪ አቶ ይሁን አሰፋ፣ የየም ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሽመልስ እጅጉ፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው ተጋባዥ እንግዶች እንዲሁም የብሄረሰቡ ተወላጆች በተገኙበት የየም ብሔረሰብ ዘመን መለወጫ “ሄቦ” በዓል በመከበር ላይ ነው።
የሄቦ በዓል ከጭጋግና ከጨለማ ወደ ብርሃን፣ ከአሮጌው ወደ አዲሱ ምዕራፍ መሻገሪያና በጉጉት የሚጠበቅ በዓል ሲሆን በተለያየ ምክንያት ከአካባቢው እርቀው የሚኖሩ የብሔረሰቡ ተወላጆች የሚገናኙበት፣ የተጣላ የሚታረቅበት፣ ታላቅ በዓል መሆኑ ይገለፃል።
ዘጋቢ: ፋሲል ኃይሉ
More Stories
“አንድነታችንን በማጎልበት የህዝብ ጥቅም የሚያስቀድም ፖለቲካ ማራመድ ይጠበቅብናል” ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ
የሕብረ-ብሔራዊ አንድነት መጠናከር መሰረት የሆነው ብዝሃነትን በአግባቡ የማስተናገድ ሂደት ዘርፈ ብዙ ፋይዳ ያለው መሆኑ ተገለፀ
በክረምቱ ወራት ሊከሰቱ የሚችሉ የተለያዩ አደጋዎችን ለመከላከል አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ላይ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ገለጸ