የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቡቶ አኒቶ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ሞገስ ባልቻ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ረዳት የመንግስት ተጠሪ አቶ ይሁን አሰፋ፣ የየም ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሽመልስ እጅጉ፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው ተጋባዥ እንግዶች እንዲሁም የብሄረሰቡ ተወላጆች በተገኙበት የየም ብሔረሰብ ዘመን መለወጫ “ሄቦ” በዓል በመከበር ላይ ነው።
የሄቦ በዓል ከጭጋግና ከጨለማ ወደ ብርሃን፣ ከአሮጌው ወደ አዲሱ ምዕራፍ መሻገሪያና በጉጉት የሚጠበቅ በዓል ሲሆን በተለያየ ምክንያት ከአካባቢው እርቀው የሚኖሩ የብሔረሰቡ ተወላጆች የሚገናኙበት፣ የተጣላ የሚታረቅበት፣ ታላቅ በዓል መሆኑ ይገለፃል።
ዘጋቢ: ፋሲል ኃይሉ
More Stories
ዲጂታል ኢትዮጵያን የመፍጠሪያ ጊዜን በማፋጠን ኢትዮጵያን የመጪው ዘመን መሪ ለማድረግ በትኩረት መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
የሆሳዕና እናት ቃለ ህይወት ቤተክርስቲያን አዲሱን ዓመት ምክንያት በማድረግ ከአንድ መቶ በላይ ለሚሆኑ አቅመ ደካሞች የምግብ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገች
እመርታ ለዘላቂ ከፍታ!