የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቡቶ አኒቶ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ሞገስ ባልቻ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ረዳት የመንግስት ተጠሪ አቶ ይሁን አሰፋ፣ የየም ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሽመልስ እጅጉ፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው ተጋባዥ እንግዶች እንዲሁም የብሄረሰቡ ተወላጆች በተገኙበት የየም ብሔረሰብ ዘመን መለወጫ “ሄቦ” በዓል በመከበር ላይ ነው።
የሄቦ በዓል ከጭጋግና ከጨለማ ወደ ብርሃን፣ ከአሮጌው ወደ አዲሱ ምዕራፍ መሻገሪያና በጉጉት የሚጠበቅ በዓል ሲሆን በተለያየ ምክንያት ከአካባቢው እርቀው የሚኖሩ የብሔረሰቡ ተወላጆች የሚገናኙበት፣ የተጣላ የሚታረቅበት፣ ታላቅ በዓል መሆኑ ይገለፃል።
ዘጋቢ: ፋሲል ኃይሉ

More Stories
የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶችን የስነ ተዋልዶ ጤና ችግሮች ለመቅረፍ የተጀመሩ ጥረቶችን ለማጎልበት የጤና አደረጃጀቶችን ሚና ማሳደግ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመግባት ዕድል ያገኙ ተማሪዎች የበለጠ ውጤታማ ለመሆን ትምህርታቸው ላይ ብቻ ሊያተኩሩ እንደሚገባ መልዕክት ተላለፈ
የሀዲያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለ2018 በጀት ዓመት ከ10 ቢልዮን ብር በላይ በጀት ለተለያዩ የልማት ስራዎች እንዲውል በተገቢው እንደሚሠራ ገለፀ