የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቡቶ አኒቶ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ሞገስ ባልቻ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ረዳት የመንግስት ተጠሪ አቶ ይሁን አሰፋ፣ የየም ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሽመልስ እጅጉ፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው ተጋባዥ እንግዶች እንዲሁም የብሄረሰቡ ተወላጆች በተገኙበት የየም ብሔረሰብ ዘመን መለወጫ “ሄቦ” በዓል በመከበር ላይ ነው።
የሄቦ በዓል ከጭጋግና ከጨለማ ወደ ብርሃን፣ ከአሮጌው ወደ አዲሱ ምዕራፍ መሻገሪያና በጉጉት የሚጠበቅ በዓል ሲሆን በተለያየ ምክንያት ከአካባቢው እርቀው የሚኖሩ የብሔረሰቡ ተወላጆች የሚገናኙበት፣ የተጣላ የሚታረቅበት፣ ታላቅ በዓል መሆኑ ይገለፃል።
ዘጋቢ: ፋሲል ኃይሉ

More Stories
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተጀመረ
የተቀናጀ የመሬት አጠቃቀም ዕቅድ ያረጁ ቡናዎችን ለማደስና አዲስ ተከላን ለማስፋፋት ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ
የስራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ተቋማትን አቅም የሚያሳድግ የ12.8 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረገ