ሀዋሳ፡ መስከረም 21/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የስልጤ ዞን አስተዳደር ከወራቤ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የምሁራን የምክክር መድረክ “የምሁራን ሚና ለህብረተሰብ ለውጥ” በሚል መሪ ቃል በወረቤ ከተማ ማካሄድ ጀምሯል፡፡
በውይይት መድረኩ ምሁራን፣ የእምነት አባቶች፣ የዞን እና የወረዳ ባለድርሻ አካላትና ተጋበዥ እንግዶች ተገኝተዋል፡፡
በምክክር መድረኩ እንኳን ደህና መጣችሁ መልክት ያስተላለፉት የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘይኔ ቢልካ፤ የዞኑን ህዝብ ልማት፣ እድገትና ባህል በማጎልበት ረገድ በምክንያታዊ ሀሳብ በማገዝ እና በጋራ በመስራት ምሁራን የበኩላቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡
ዘጋቢ: ሳጂዳ ሙዳስር – ከሆሳዕና ጣቢያችን
More Stories
ዲጂታል ኢትዮጵያን የመፍጠሪያ ጊዜን በማፋጠን ኢትዮጵያን የመጪው ዘመን መሪ ለማድረግ በትኩረት መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
የሆሳዕና እናት ቃለ ህይወት ቤተክርስቲያን አዲሱን ዓመት ምክንያት በማድረግ ከአንድ መቶ በላይ ለሚሆኑ አቅመ ደካሞች የምግብ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገች
እመርታ ለዘላቂ ከፍታ!