ሀዋሳ፡ መስከረም 21/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የስልጤ ዞን አስተዳደር ከወራቤ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የምሁራን የምክክር መድረክ “የምሁራን ሚና ለህብረተሰብ ለውጥ” በሚል መሪ ቃል በወረቤ ከተማ ማካሄድ ጀምሯል፡፡
በውይይት መድረኩ ምሁራን፣ የእምነት አባቶች፣ የዞን እና የወረዳ ባለድርሻ አካላትና ተጋበዥ እንግዶች ተገኝተዋል፡፡
በምክክር መድረኩ እንኳን ደህና መጣችሁ መልክት ያስተላለፉት የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘይኔ ቢልካ፤ የዞኑን ህዝብ ልማት፣ እድገትና ባህል በማጎልበት ረገድ በምክንያታዊ ሀሳብ በማገዝ እና በጋራ በመስራት ምሁራን የበኩላቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡
ዘጋቢ: ሳጂዳ ሙዳስር – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
ህብር ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የምርጫ ማኒፌስቶ፣ የዕጩ ማስተዋወቂያ እንዲሁም የምርጫ ቅስቀሳ ፕሮግራም በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ አካሄደ
ኦርቢስ ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ ጥራት ያለው የአይን ህክምና በሀገሪቱ ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየሰራ መሆኑ ተገለፀ
ብልጽግና ፓርቲ የማህበረሰቡ ችግር የሚቀርፉ ፕሮጀክቶችን ገንብቶ በማጠናቀቅ በውጤታማነት ለአገልግሎት እያበቃ ነው – ዶ/ር መሀመድ ኑርዬ