ሀዋሳ፡ መስከረም 21/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የስልጤ ዞን አስተዳደር ከወራቤ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የምሁራን የምክክር መድረክ “የምሁራን ሚና ለህብረተሰብ ለውጥ” በሚል መሪ ቃል በወረቤ ከተማ ማካሄድ ጀምሯል፡፡
በውይይት መድረኩ ምሁራን፣ የእምነት አባቶች፣ የዞን እና የወረዳ ባለድርሻ አካላትና ተጋበዥ እንግዶች ተገኝተዋል፡፡
በምክክር መድረኩ እንኳን ደህና መጣችሁ መልክት ያስተላለፉት የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘይኔ ቢልካ፤ የዞኑን ህዝብ ልማት፣ እድገትና ባህል በማጎልበት ረገድ በምክንያታዊ ሀሳብ በማገዝ እና በጋራ በመስራት ምሁራን የበኩላቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡
ዘጋቢ: ሳጂዳ ሙዳስር – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
የሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ በስፖርትና ባህል ልማት ዘርፍ የሚገኘውን ተጠቃሚነት ለማሳደግ አበክሮ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
ህግና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን ፍትህ ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት ሥራ አፈፃፀም አደመጠ
ከተማዋን ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ እንደሚሠራ የዲላ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ