ሀዋሳ፡ መስከረም 21/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የስልጤ ዞን አስተዳደር ከወራቤ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የምሁራን የምክክር መድረክ “የምሁራን ሚና ለህብረተሰብ ለውጥ” በሚል መሪ ቃል በወረቤ ከተማ ማካሄድ ጀምሯል፡፡
በውይይት መድረኩ ምሁራን፣ የእምነት አባቶች፣ የዞን እና የወረዳ ባለድርሻ አካላትና ተጋበዥ እንግዶች ተገኝተዋል፡፡
በምክክር መድረኩ እንኳን ደህና መጣችሁ መልክት ያስተላለፉት የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘይኔ ቢልካ፤ የዞኑን ህዝብ ልማት፣ እድገትና ባህል በማጎልበት ረገድ በምክንያታዊ ሀሳብ በማገዝ እና በጋራ በመስራት ምሁራን የበኩላቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡
ዘጋቢ: ሳጂዳ ሙዳስር – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተጀመረ
የተቀናጀ የመሬት አጠቃቀም ዕቅድ ያረጁ ቡናዎችን ለማደስና አዲስ ተከላን ለማስፋፋት ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ
የስራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ተቋማትን አቅም የሚያሳድግ የ12.8 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረገ