ለሠራተኞች ጠንካራ የሥራ ባህልና ምቹ የስራ ቦታ መፍጠር ይገባል ሲልም ቢሮው አመልክቷል ፡፡
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ዋኖ ዋሎሌ ለስራ ፈላጊ ዜጎች በሀገር ውስጥና የውጪ ሀገር የስራ ዕድል እንዲፈጠር ሲደረግ መቆየቱን ተናግረዋል።
ማህረሰብን መሠረት ያደረገ የማህበራዊ ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችሉ ተግባራት ሲከናወኑ መቆየታቸውን የሚናገሩት የቢሮው ኃላፊ በዚህም ለችግር ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን በመለየት የሀገር ውስጥና የውጪ የስራ ዕድል እንዲመቻችላቸውም ተደርጓልም ብለዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ቤሔረሰቦች ም/ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አዳማ ትንጳኤ በበኩላቸው በክልሉ የሠራተኛና አሠሪዎች እንቅስቃሴ ትርጉም ባለው መልኩ ተጠቃሚነት ላይ በማተኮር በስልጠና ላይ መሠረት ያደረገ ስራ ሊሠራ ይገባል ብለዋል።
የህፃናት ጉልበት ብዝበዛ በክልሉ በሰፊው የሚስተዋል ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ባለድርሻ አካላት ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት የሚደረጉ ጥረቶችን ሊያግዙ ይገባልም ብለዋል።
በይበልጥ ህጋዊ የሀገር ውስጥ የስራ ስምሪትን ተግባራዊ በማድረግ ከስራ እድል ፈጠራ በተጨማሪ ህገወጥ የሰዎች ዝውውርን መከላከልም ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባም አመላክተዋል።
ህገ ወጥ የህፃናት ጉልበት ብዝበዛ አሁንም በክልሉ በሰፊው የሚስተዋል ነው ያሉት አቶ አዳማ የህብረተሰቡን ግንዛቤን በማሳደግ ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት ጥረት ሊደረግ ይገባልም ብለዋል።
በተጠናቀቀው በጀት አመት ከ21 ሺህ 6 መቶ በላይ በክልሉ የሚገኙ ዜጎች በውጪ ሀገራት የስራ ዕድል እንዲያገኙ መደረጉም ከቢሮ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
የቢሮው የ2016 በጀት አመት አፈፃፀምና የ2017 እቅድ ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ በአርባምንጭ ከተማ ተካሂዷል።
ዘጋቢ : በኃይሉ ሙሉጌታ

More Stories
የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶችን የስነ ተዋልዶ ጤና ችግሮች ለመቅረፍ የተጀመሩ ጥረቶችን ለማጎልበት የጤና አደረጃጀቶችን ሚና ማሳደግ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመግባት ዕድል ያገኙ ተማሪዎች የበለጠ ውጤታማ ለመሆን ትምህርታቸው ላይ ብቻ ሊያተኩሩ እንደሚገባ መልዕክት ተላለፈ
የሀዲያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለ2018 በጀት ዓመት ከ10 ቢልዮን ብር በላይ በጀት ለተለያዩ የልማት ስራዎች እንዲውል በተገቢው እንደሚሠራ ገለፀ