ሀዋሳ፡ መስከረም 20/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የትምህርት ጥራትን በማስጠበቅ በዘርፉ የተፈለገውን ውጤት ለማምጣት የድጋፍና ክትትል ሥራዎች ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የጌዴኦ ዞን አስተዳዳር አስታወቀ፡፡
የጌዴኦ ዞን አስተዳደር የሥራ ኃላፊዎች የትምህርት ሳምንትን ምክንያት በማድረግ በዲላ ከተማ በሚገኙ ትምህርት ቤቶች የመማር ማስተማር ሂደትን ምልከታ አድርገዋል፡፡
ምልከታው ” ትምህርት ለሁሉም ” የትምህርት ሳምንትን ምክንያትን በማድረግ የተከናወነ መሆኑም ተመላክቷል።
በተደረገው ምልከታ የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳደር ዶ/ር ዝናቡ ወልዴ፤ በትምህርት ሥራ የተፈለገውን ውጤት ለማስመዝገብ ባለድርሻ አካላት የቅርብ ክትትል በማድረግ መስራት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል፡፡
በዞኑ በትምህርት ዘርፍ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ ለማድረግ የተለያዩ ተግባራትን በማከናወን ላይ መሆናቸውን የገለጹት አስተዳዳሪው፥ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
ለዚህም የዘርፉ አመራር አካላት ከመቼውም ጊዜ በላይ ቁርጠኛ አቋም በመውሰድ ለእቅዱ መሳካት የድርሻውን ሊወጡ እንደሚገባም ዶክተር ዝናቡ አሳስበዋል።
በቀጣይ ጥቂት ጊዜያትም ህብረተሰቡን በተለያዩ እርከኖች በማወያየት የተያዘውን እቅድ በማሳካት ትምህርትን ለበርካቶች ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየተሠራ መሆኑንም ከከተማው ትምህርት ጽህፈት ቤት የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
በምልከታ መርሃ ግብር የዞኑ የሥራ ኃላፊዎች፣ የከተማው አመራሮችና የትምህርት ዘርፍ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል፡፡
ዘጋቢ፡ እምነት ሽፈራው – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
የትምህርት ጥራት በማስጠበቅ በዘርፉ የተፈለገውን ውጤት ለማምጣት የድጋፍና ክትትል ሥራዎች ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተገለጸ
ሀዋሳ፡ መስከረም 20/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የትምህርት ጥራትን በማስጠበቅ በዘርፉ የተፈለገውን ውጤት ለማምጣት የድጋፍና ክትትል ሥራዎች ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የጌዴኦ ዞን አስተዳዳር አስታወቀ፡፡
የጌዴኦ ዞን አስተዳደር የሥራ ኃላፊዎች የትምህርት ሳምንትን ምክንያት በማድረግ በዲላ ከተማ በሚገኙ ትምህርት ቤቶች የመማር ማስተማር ሂደትን ምልከታ አድርገዋል፡፡
ምልከታው ” ትምህርት ለሁሉም ” የትምህርት ሳምንትን ምክንያትን በማድረግ የተከናወነ መሆኑም ተመላክቷል።
በተደረገው ምልከታ የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳደር ዶ/ር ዝናቡ ወልዴ፤ በትምህርት ሥራ የተፈለገውን ውጤት ለማስመዝገብ ባለድርሻ አካላት የቅርብ ክትትል በማድረግ መስራት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል፡፡
በዞኑ በትምህርት ዘርፍ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ ለማድረግ የተለያዩ ተግባራትን በማከናወን ላይ መሆናቸውን የገለጹት አስተዳዳሪው፥ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
ለዚህም የዘርፉ አመራር አካላት ከመቼውም ጊዜ በላይ ቁርጠኛ አቋም በመውሰድ ለእቅዱ መሳካት የድርሻውን ሊወጡ እንደሚገባም ዶክተር ዝናቡ አሳስበዋል።
በቀጣይ ጥቂት ጊዜያትም ህብረተሰቡን በተለያዩ እርከኖች በማወያየት የተያዘውን እቅድ በማሳካት ትምህርትን ለበርካቶች ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየተሠራ መሆኑንም ከከተማው ትምህርት ጽህፈት ቤት የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
በምልከታ መርሃ ግብር የዞኑ የሥራ ኃላፊዎች፣ የከተማው አመራሮችና የትምህርት ዘርፍ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል፡፡
ዘጋቢ፡ እምነት ሽፈራው – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
ህዝበ ሙስሊሙ የመውሊድ በዓልን ሲያከብር በብዝሃነት ውስጥ የሚንፀባረቁ የመረዳዳትና የአብሮነት በጎ እሴቶችን ይበልጥ በማጠናከር ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ኃላፊና የየዞን ከፍተኛ አመራሮች በሣውላ ማረሚያ ተቋም አረንጓዴ አሻራቸውን በማኖር ልዩ ልዩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ
በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር ምርመራ እና ልየታ ተካሄደ