አቅመ ደካሞችን በመርዳት እና በመተጋገዝ በአብሮነት መስራት እንደሚገባ ቢሮው ገልጿል፡፡
በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የተለያዩ ተግባራት ሲከናወኑ ቆይተዋል፡፡
የዱቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንገዶች ባለስልጣን ምክትል የቢሮ ሀላፊ አቶ ኢያሱ ኢትሳ እና የቢሮው ማኔጅመንት አባላት በአሌ ዞን ኮላንጎ ከተማ አስተዳደር በመገኘት ለአንዲት አቅመ ደካማ እናት ከ1 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የመኖሪያ ቤት ግንባታ አካሄደ፡፡
በቦታው ተገኝተው የቤት ግንባታ መርሃ ግብሩን ያስጀመሩት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንገዶች ባለስልጣን ምክትል የቢሮ ኃላፊና ተወካይ አቶ ኢሳያስ ቢፍቱ፤ ቢሮው በየአመቱ የአቅመ ደካሞችን ቤት እየገነባ መቆየቱን ገልፀዋል።
አሁንም በአሌ ዞን ኮላንጎ ከተማ አስተዳደር በመገኘት በ45 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈ ደረጃውን የጠበቀ የመኖሪያ ቤት ግንባታ ማስጀመራቸውን ተናግረዋል፡፡
አክለውም የበጎ ተግባር ስራ ከህሊና እርካታ ባለፈ በፈጣሪ ዘንድም ጽድቅ በመሆኑ እርስ በእርስ ለመደጋገፍ ለኢትዮጵያ ከፍታ እንረባረብ ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
የአሌ ዞን ምክትል ዋና አስተዳዳሪ እና የኢኮኖሚ ክላስተር አስተባባሪ አቶ እያሱ ኢትሳ፤ የክልሉ መንገዶች ባለስልጣን ላደረገው በጎ ተግባር በዞኑ ስም አመስግነዋል፡፡
ባለቤታቸውን በሞት ያጡት እና የ5 ልጆች እናት የሆኑት ወ/ሮ አስቴር መገርሳ በተደረገላቸው ድጋፍ መደሰታቸውን ገልፀው የክልሉን መንገዶች ባለስልጣን እና የማናጅመንት አባላትን አመስግነዋል፡፡
ለግንባታው የሚያስፈልጉ ቁሳቁሶች ተሟልተው መቅረባቸውም ተመላክቷል፡፡
ዘጋቢ፡ ገነት መኮንን – ከአርባምንጭ ጣቢያችን
More Stories
“አንድነታችንን በማጎልበት የህዝብ ጥቅም የሚያስቀድም ፖለቲካ ማራመድ ይጠበቅብናል” ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ
የሕብረ-ብሔራዊ አንድነት መጠናከር መሰረት የሆነው ብዝሃነትን በአግባቡ የማስተናገድ ሂደት ዘርፈ ብዙ ፋይዳ ያለው መሆኑ ተገለፀ
በክረምቱ ወራት ሊከሰቱ የሚችሉ የተለያዩ አደጋዎችን ለመከላከል አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ላይ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ገለጸ