የዞኑ አስተዳደር የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር መክሯል።
በዞኑ አንዳንድ አካባቢዎች የሚስተዋሉ የዉሃ አካላት ብክለትን ለመከላከል በትብብር እንደሚሰራ የኣሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ተወካይ አቶ ሳምሶን ግቅሺ ገልጸዋል።
ሀላፊው አክለውም የድምፅ ብክለትን ለመከላከል በጋራ ጥረት ማድረግ እንደሚገባም ተናግረዋል።
የጂንካ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሲሳይ ጋልሺ በበኩላቸው በከተማው የቆሻሻ ማስወገጃዎችን በመለየት በዘርፉ ከሚሰሩ ባለድርሻ አካላት ጋር እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።
ከወራጅ ዉሃ ብክለት ጋር ተያይዞ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍና የፕላስቲክ ቆሻሻዎችን ለማስወገድ በየደረጃው አደረጃጀቶችን በማጠናከር እንደሚሰራም ከንቲባው ተናግረዋል።
በእምነት ተቋማትና በግለሰቦች አማካኝነት የድምፅ ብክለት እያየለ በመምጣቱ ሥርዓት ሊበጅለት እንደሚገባ ከንቲባው አመላክተዋል።
በኣሪ ዞን ደንና አካባቢ ጥበቃ ፅህፈት ቤት የአካባቢ ጥበቃ ቡድን መሪ አቶ ኑሬሳ መርኪና እንደገለፁት የአካባቢ ብክለት የሰው ልጆች በሚያከናዉኗቸዉ አንዳንድ ተግባራት ጋር ተያይዞ የሚከሰት በመሆኑ ችግሩን ለመከላከል ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ ይገባል።
ከጂንካ ከተማ ነዋሪዎች መካከል መምህር ፋንታው እሸቱና ሌሎችም በሰጡት አስተያየት የድምፅ እና የአካባቢ ብክለትን ለመከላከል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠል አለባቸው ብለዋል።
ዘጋቢ፡ ዳኜ ጥላሁን – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
ህዝበ ሙስሊሙ የመውሊድ በዓልን ሲያከብር በብዝሃነት ውስጥ የሚንፀባረቁ የመረዳዳትና የአብሮነት በጎ እሴቶችን ይበልጥ በማጠናከር ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ኃላፊና የየዞን ከፍተኛ አመራሮች በሣውላ ማረሚያ ተቋም አረንጓዴ አሻራቸውን በማኖር ልዩ ልዩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ
በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር ምርመራ እና ልየታ ተካሄደ