የመስቀል በዓል ገበያ የበሬ ዋጋ ከአዲሱ ዓመት የበዓል ገበያ ጋር ሲነፃፀር ጭማሪ እንዳለው በሀዋሳ ከተማ 01 ቀበሌ በሚገኘው የቁም ከብት ገበያ ገዢዎችና ነጋዴዎች ተናገሩ::
አቶ ጌታሁን ሻንካ፣ ወ/ሮ አበባ ካሳዬ እና አቶ ስዩም ጥላሁን የሀዋሳ ከተማ ነዋሪዎች ሲሆኑ በማህበር ለመስቀል በዓል ያጠራቀሙትን ገንዘብ ሀዋሳ 01 ቀበሌ በሚገኘው የቁም ከብት ገበያ ለመግዛት በመጡበት አጋጣሚ ነው ያገኘናቸው::
የመስቀል የእርድ በሬ ገበያ ከአምናው የዋጋ ጭማሪ እንዳለው ጠቁመው ከፍተኛው 120 ሺህ፣ መካከለኛው 75 ሺህ እንዲሁም ዝቅተኛው 65 ሺህ እንደሚገዛ ነው የገለፁት::
አቶ ጌታሁን ሻንካ እንደተናገሩት ዓመቱን ሙሉ ለመስቀል በዓል የቆጠቡትን ገንዘብ በማውጣት ጥሩ የሚባል ለቁርጥና ለክትፎ የሚሆን በሬ በ75 ሺህ ብር ገዝተዋል::
ወ/ሮ እልፍነሽ ሴዴቦ በበኩላቸው የእርድ በሬ በብዛት የገባ ቢሆንም ከአዲስ አመት ጋር ሲነፃፀር የ10 ሺህ ብር ጭማሬ እንዳጋጠማቸው ተናግረዋል::
የበግና የፍየል ዋጋ ሲተይ ደግሞ ከፍተኛው 20 ሺህ፣ መካከለኛው 10 ሺህ እንዲሁም ዝቅተኛው 4ሺ 500 እንደሆነ የተናገሩት አቶ ትዕግስቱ አበራ ናቸው::
አቶ ወንድሙ ወጋሶ የእርድ በሬ ነጋዴ ሲሆኑ በዛሬው ገበያ የዋጋ ልዩነት እንዳለው ጠቁመዋል፡፡
ሸማቾቹ ሲናገሩ የመስቀል በአል ተከፋፍለን በፍቅርና በደስታ የምናከብረው በዓል እንደመሆኑ መጠን አቅመ ደካሞችን በማሰብ ያለንን ማካፈል ይጠበቅብናል ብለዋል::
ሸማቾቹ ሀገራችንን ፈጣሪ ሰላም እንዲያደርጋት በመመኘት ለክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለመስቀል በዓል በሰላም አደረሳችሁ ብለዋል::
ዘጋቢ: ሐና በቀለ

More Stories
ህዝበ ሙስሊሙ የመውሊድ በዓልን ሲያከብር በብዝሃነት ውስጥ የሚንፀባረቁ የመረዳዳትና የአብሮነት በጎ እሴቶችን ይበልጥ በማጠናከር ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ኃላፊና የየዞን ከፍተኛ አመራሮች በሣውላ ማረሚያ ተቋም አረንጓዴ አሻራቸውን በማኖር ልዩ ልዩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ
በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር ምርመራ እና ልየታ ተካሄደ