ሀዋሳ፡ መስከረም 13/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የከተማና መሠረተ ልማት ሚንስቴር የከተማ መሠረተ ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዋኖ ዋኬና የአለም ባንክ ካንትሪ ዳይሬክተር ሚስተር ማርቲን ኦንችያ የተመራ ሉዑክ ለሥራ ጉዳይ ወደ ኣሪ ዞን ጂንካ ከተማ ገብተዋል።
ሉዑካን ቡድኑ ጂንካ አየር ማረፍያ ሲደርሱ የኣሪ ዞን አሰተዳደር ተወካይ አቀባበል አድርጎላቸዋል።
በቆይታቸውም በጂንካ ከተማ በመንግስትና በአለም ባንክ ድጋፍ እየተተገበሩ ያሉ ሥራዎችን ጉብኝትና ከባለድርሻ አካላት ጋር ወይይት በማድረግ ቀጣይ ሥራ ዙርያ የጋራ መግባቢያ እንደሚደረግ ታውቋል።
ዘጋቢ: ከተማ በየነ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በክልሉ ለሚገኙ የዘርፉ ባለሙያዎች ስልጠና መስጠት ጀመረ
የቅድመ በሽታ መከላከል ተግባራትን በአግባቡ በመፈፀም ጤናማ ትውልድ ለመፍጠር በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የሸዋል ዒድ (ቀሊ ፍቼ) ባህላዊ ስርዓት በስልጤ