ሀዋሳ፡ መስከረም 13/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የከተማና መሠረተ ልማት ሚንስቴር የከተማ መሠረተ ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዋኖ ዋኬና የአለም ባንክ ካንትሪ ዳይሬክተር ሚስተር ማርቲን ኦንችያ የተመራ ሉዑክ ለሥራ ጉዳይ ወደ ኣሪ ዞን ጂንካ ከተማ ገብተዋል።
ሉዑካን ቡድኑ ጂንካ አየር ማረፍያ ሲደርሱ የኣሪ ዞን አሰተዳደር ተወካይ አቀባበል አድርጎላቸዋል።
በቆይታቸውም በጂንካ ከተማ በመንግስትና በአለም ባንክ ድጋፍ እየተተገበሩ ያሉ ሥራዎችን ጉብኝትና ከባለድርሻ አካላት ጋር ወይይት በማድረግ ቀጣይ ሥራ ዙርያ የጋራ መግባቢያ እንደሚደረግ ታውቋል።
ዘጋቢ: ከተማ በየነ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
የሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ በስፖርትና ባህል ልማት ዘርፍ የሚገኘውን ተጠቃሚነት ለማሳደግ አበክሮ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
ህግና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን ፍትህ ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት ሥራ አፈፃፀም አደመጠ
ከተማዋን ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ እንደሚሠራ የዲላ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ