ሀዋሳ፡ መስከረም 13/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የከተማና መሠረተ ልማት ሚንስቴር የከተማ መሠረተ ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዋኖ ዋኬና የአለም ባንክ ካንትሪ ዳይሬክተር ሚስተር ማርቲን ኦንችያ የተመራ ሉዑክ ለሥራ ጉዳይ ወደ ኣሪ ዞን ጂንካ ከተማ ገብተዋል።
ሉዑካን ቡድኑ ጂንካ አየር ማረፍያ ሲደርሱ የኣሪ ዞን አሰተዳደር ተወካይ አቀባበል አድርጎላቸዋል።
በቆይታቸውም በጂንካ ከተማ በመንግስትና በአለም ባንክ ድጋፍ እየተተገበሩ ያሉ ሥራዎችን ጉብኝትና ከባለድርሻ አካላት ጋር ወይይት በማድረግ ቀጣይ ሥራ ዙርያ የጋራ መግባቢያ እንደሚደረግ ታውቋል።
ዘጋቢ: ከተማ በየነ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
ህዝበ ሙስሊሙ የመውሊድ በዓልን ሲያከብር በብዝሃነት ውስጥ የሚንፀባረቁ የመረዳዳትና የአብሮነት በጎ እሴቶችን ይበልጥ በማጠናከር ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ኃላፊና የየዞን ከፍተኛ አመራሮች በሣውላ ማረሚያ ተቋም አረንጓዴ አሻራቸውን በማኖር ልዩ ልዩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ
በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር ምርመራ እና ልየታ ተካሄደ