ሀዋሳ፡ መስከረም 13/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የከተማና መሠረተ ልማት ሚንስቴር የከተማ መሠረተ ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዋኖ ዋኬና የአለም ባንክ ካንትሪ ዳይሬክተር ሚስተር ማርቲን ኦንችያ የተመራ ሉዑክ ለሥራ ጉዳይ ወደ ኣሪ ዞን ጂንካ ከተማ ገብተዋል።
ሉዑካን ቡድኑ ጂንካ አየር ማረፍያ ሲደርሱ የኣሪ ዞን አሰተዳደር ተወካይ አቀባበል አድርጎላቸዋል።
በቆይታቸውም በጂንካ ከተማ በመንግስትና በአለም ባንክ ድጋፍ እየተተገበሩ ያሉ ሥራዎችን ጉብኝትና ከባለድርሻ አካላት ጋር ወይይት በማድረግ ቀጣይ ሥራ ዙርያ የጋራ መግባቢያ እንደሚደረግ ታውቋል።
ዘጋቢ: ከተማ በየነ – ከጂንካ ጣቢያችን
More Stories
“አንድነታችንን በማጎልበት የህዝብ ጥቅም የሚያስቀድም ፖለቲካ ማራመድ ይጠበቅብናል” ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ
የሕብረ-ብሔራዊ አንድነት መጠናከር መሰረት የሆነው ብዝሃነትን በአግባቡ የማስተናገድ ሂደት ዘርፈ ብዙ ፋይዳ ያለው መሆኑ ተገለፀ
በክረምቱ ወራት ሊከሰቱ የሚችሉ የተለያዩ አደጋዎችን ለመከላከል አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ላይ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ገለጸ