ሀዋሳ፡ መስከረም 11/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የሃዲያ ብሔር ዘመን መለወጫ ያሆዴ በዓል የአደባባይ አከባበር በሆሳዕና ከተማ በሀድይ ናፈራ እየተካሄደ ይገኛል።
በኢፌዲሪ የባህልና ስፖርት ሚኒስተር ዴኤታ አቶ አስፋው አዛሉ፣ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ባህልና ቱርዝም ቢሮ የቢሮ ምክትል ኃላፊና የባህል ዘርፍ ኃላፊ አቶ ደግነህ ቦጋለ፣ የሀድያ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ ዶክተር በፈቃዱ ገ/ሃና፣ የዞኑ ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ ወይዘሮ እቴነሽ ሙሉጌታ፣ የባህል ሽመግሌዎች፣ ከሀገሪቱ ከተለያዩ አካባቢዎች የተጋበዙ እንግዶች፣ የሆሳዕና ከተማና የሁሉም የዞኑ መዋቅር ነዋሪዎችና የብሔሩ ተወላጆች እየታደሙ ይገኛል።
የበዓሉ አከባበር ስነ ስርዓት የተጀመረው ሰሞኑን ከዚህ ዓለም በሞት ለተለዩት ለሀንሳር ጋራድ ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ የአንድ ደቂቃ የህሊና ፀሎት በማድረግ ነው።
ዘጋቢ፡ ኤርጡሜ ዳንኤል – ከሆሳዕና ጣቢያችን
More Stories
የፖሊስ አባላትና ሲቪል ሠራተኞች የገንዘብ ቁጠባና ብድር ህብረት ሥራ ማህበር ጠቅላላ ጉባኤውን አካሄደ
ኢትዮ-ኮደርስ ኢንሼቲቭ ዲጅታል ክህሎትን በማስጨበጥ ተወዳዳሪነትን የሚያሳድግ መሆኑ ተገለጸ
ስራ አጥነትን ደረጃ በደረጃ ለመቀነስና ምርታማነትን ከፍ ለማድረግ የባለድርሻ ተቋማት የተቀናጀ ርብርብ እንደሚሻ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስራ እድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት ቢሮ ገለጸ