የሃዲያ ብሔር ዘመን መለወጫ ያሆዴ በዓል  የአደባባይ  አከባበር  በሆሳዕና ከተማ በሀድይ ናፈራ እየተካሄደነው

ሀዋሳ፡ መስከረም 11/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የሃዲያ ብሔር ዘመን መለወጫ ያሆዴ በዓል  የአደባባይ  አከባበር  በሆሳዕና ከተማ በሀድይ ናፈራ እየተካሄደ ይገኛል።

በኢፌዲሪ የባህልና ስፖርት ሚኒስተር ዴኤታ አቶ አስፋው አዛሉ፣ በማዕከላዊ   ኢትዮጵያ ክልል ባህልና ቱርዝም ቢሮ የቢሮ ምክትል ኃላፊና የባህል ዘርፍ ኃላፊ አቶ ደግነህ ቦጋለ፣ የሀድያ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ ዶክተር በፈቃዱ ገ/ሃና፣ የዞኑ ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ ወይዘሮ እቴነሽ ሙሉጌታ፣ የባህል ሽመግሌዎች፣ ከሀገሪቱ ከተለያዩ አካባቢዎች የተጋበዙ እንግዶች፣ የሆሳዕና ከተማና የሁሉም የዞኑ መዋቅር ነዋሪዎችና የብሔሩ ተወላጆች እየታደሙ ይገኛል።

የበዓሉ አከባበር ስነ ስርዓት የተጀመረው ሰሞኑን ከዚህ ዓለም በሞት ለተለዩት ለሀንሳር ጋራድ ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ የአንድ ደቂቃ የህሊና ፀሎት በማድረግ ነው።

ዘጋቢ፡ ኤርጡሜ ዳንኤል – ከሆሳዕና ጣቢያችን