ሀዋሳ፡ መስከረም 11/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የሃዲያ ብሔር ዘመን መለወጫ ያሆዴ በዓል የአደባባይ አከባበር በሆሳዕና ከተማ በሀድይ ናፈራ እየተካሄደ ይገኛል።
በኢፌዲሪ የባህልና ስፖርት ሚኒስተር ዴኤታ አቶ አስፋው አዛሉ፣ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ባህልና ቱርዝም ቢሮ የቢሮ ምክትል ኃላፊና የባህል ዘርፍ ኃላፊ አቶ ደግነህ ቦጋለ፣ የሀድያ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ ዶክተር በፈቃዱ ገ/ሃና፣ የዞኑ ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ ወይዘሮ እቴነሽ ሙሉጌታ፣ የባህል ሽመግሌዎች፣ ከሀገሪቱ ከተለያዩ አካባቢዎች የተጋበዙ እንግዶች፣ የሆሳዕና ከተማና የሁሉም የዞኑ መዋቅር ነዋሪዎችና የብሔሩ ተወላጆች እየታደሙ ይገኛል።
የበዓሉ አከባበር ስነ ስርዓት የተጀመረው ሰሞኑን ከዚህ ዓለም በሞት ለተለዩት ለሀንሳር ጋራድ ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ የአንድ ደቂቃ የህሊና ፀሎት በማድረግ ነው።
ዘጋቢ፡ ኤርጡሜ ዳንኤል – ከሆሳዕና ጣቢያችን
More Stories
“አንድነታችንን በማጎልበት የህዝብ ጥቅም የሚያስቀድም ፖለቲካ ማራመድ ይጠበቅብናል” ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ
የሕብረ-ብሔራዊ አንድነት መጠናከር መሰረት የሆነው ብዝሃነትን በአግባቡ የማስተናገድ ሂደት ዘርፈ ብዙ ፋይዳ ያለው መሆኑ ተገለፀ
በክረምቱ ወራት ሊከሰቱ የሚችሉ የተለያዩ አደጋዎችን ለመከላከል አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ላይ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ገለጸ