ሀዋሳ፡ መስከረም 10/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በባለፈው የበልግ ወቅት 669 ሄክታር መሬት በስኳር ድንች የተሸፈነ ሲሆን 178 ሺህ 354 ኩንታል ምርት እንደሚጠበቅ የኮሬ ዞን ግብርና መምሪያ የሆርቲካልቸር ልማትና ጥበቃ ዳሬክቶሬት አስታውቋል።
በኮሬ ዞን ግብርና መምሪያ የሆርቲካልቸር ልማትና ጥበቃ ዳሬክቶሬት ወ/ሮ ይደነቁ በዛብህ እንደገለጹት፥ የስኳር ድንች ተፈላጊነቱም እየጨመረ በመምጣቱ ምርቱ ወደ አጎራባች ዞኖችና ክልል እየተጫነ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
አክለውም ወይዘሮ ይደነቁ የተለያዩ ንጥረነገር ያለው ብርቱካናማ የስኳር ድንች ዝርያ የተወሰኑ ቀበሌያት ላይ ማስፋፋት መጀመራቸውን ተናግረዋል።
በዞኑ ከጋሙሌና ቆቦ ቀበሌያት ያነጋገርናቸው አርሶ አደር ደግፌ ደያሶ እና ወጣት ወለጋ ወረደ፥ ስኳር ድንች የተከሉ ሲሆኑ ዘንድሮ በቂ ዝናብ በመኖሩ ከ100 ሺህ ብር በላይ ገቢ እንደሚጠብቁ ተናግረዋል።
ስኳር ድንች በባህሪው ተኮትኩቶ ሀረግ ካወጣ በአረም የማያስቸግር እንዲሁም ያለ ማጣፈጫ የሚቀርብ በመሆኑ ለአመጋገብም ምቹ ነው ብለዋል።
የስኳር ድንች የተለያዩ የጤና ጠቀሜታዎች እንዳሉትም ይነገራል።
ዘጋቢ: ምርጫ መላኩ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
More Stories
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በደቡብ ኦሞ ዞን ኮይቤ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል አንዲት እናት በአንድ ጊዜ 3 ልጆችን ተገላገለች
ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ በድንገተኛ መሬት መንሸራተት አደጋ ለተፈናቀሉ ወገኖች በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር የተገነቡ 296 መኖርያ ቤቶችን መርቀው ለነዋሪዎች አስረከቡ
የንግድ ሥርዓትን ለማዘመን የባለድርሻ አካላት ድጋፍና ቅንጅታዊ ሥራ ወሳኝ መሆኑ ተገለፀ