የኬሌ ከተማ ዋና አፈ ጉባኤና የከተማው ከንቲባ ተወካይ ወ/ሮ ሃና ኃይሌ ድጋፍ የተደረገላቸው ተረጂዎች ጀርባ ሌሎች መኖራቸውን በማስታወስ ሁሉም ሰው የመረዳዳት ባህል ማጎልበት እንደሚገባው አስረድተዋል።
የድጋፉን ቁሳቁስ ያሰባሰቡት በኬሌ ከተማ ሴቶች፣ ህፃናትና ወጣቶች ጉዳይ ጽ/ቤት የቀድሞ ኃላፊ ወ/ሮ ርብቃ ታዬ ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ መሆኑን አስታውሰው ድጋፉን ያበረከቱ አካላትና ጊዜያቸውንና ጉልበታቸውን ሰውተው ያገለገሉ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶችን አመስግነዋል።
በኬሌ ከተማ ሴቶች፣ ህፃናትና ወጣቶች ጉዳይ ጽ/ቤት የወጣቶች ማካተትና ንቅናቄ ተሳትፎ ቡድን መሪ አቶ ዳግም ጀምቦ እንደገለጹት፤ የአልባሳትና የትምህርት ቁሳቁስ የተደረገው ለ1መቶ 20 በላይ አረጋውያን፣ ወላጅ ላጡና ለአደራ ልጆች ነው።
ዘጋቢ: ምርጫ መላኩ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
በሀሬ ተፋሰስበ በ27 ቀናት ወስጥ 35 ሄክታር መሬት ላይ እርከን ፣ አፈር እቀባና የተለያዩ ዕፅዋት ተከላ መከናወኑ ተገለፀ
አዲሱ የቦንጋ ከተማ መዋቅራዊ ፕላን የኡፋ እና የውሽውሽ ከተሞችን ያካተተ መሆኑን በሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የከተማ ልማት ዲን አቶ ደጉ በቀለ ገለጹ
የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በየዓመቱ ህዳር 29 ቀን እንዲከበር ሲወሰን ዓላማው ብሔር ብሔረሰቦች ባህሎቻቸውን በመለዋወጥ ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በማጠናከር ሃገራዊ መግባባትን እንዲፈጥሩ ማድረግ ነው – የኢፌዴሪ ፌዴሬሽን ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር