የኬሌ ከተማ ዋና አፈ ጉባኤና የከተማው ከንቲባ ተወካይ ወ/ሮ ሃና ኃይሌ ድጋፍ የተደረገላቸው ተረጂዎች ጀርባ ሌሎች መኖራቸውን በማስታወስ ሁሉም ሰው የመረዳዳት ባህል ማጎልበት እንደሚገባው አስረድተዋል።
የድጋፉን ቁሳቁስ ያሰባሰቡት በኬሌ ከተማ ሴቶች፣ ህፃናትና ወጣቶች ጉዳይ ጽ/ቤት የቀድሞ ኃላፊ ወ/ሮ ርብቃ ታዬ ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ መሆኑን አስታውሰው ድጋፉን ያበረከቱ አካላትና ጊዜያቸውንና ጉልበታቸውን ሰውተው ያገለገሉ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶችን አመስግነዋል።
በኬሌ ከተማ ሴቶች፣ ህፃናትና ወጣቶች ጉዳይ ጽ/ቤት የወጣቶች ማካተትና ንቅናቄ ተሳትፎ ቡድን መሪ አቶ ዳግም ጀምቦ እንደገለጹት፤ የአልባሳትና የትምህርት ቁሳቁስ የተደረገው ለ1መቶ 20 በላይ አረጋውያን፣ ወላጅ ላጡና ለአደራ ልጆች ነው።
ዘጋቢ: ምርጫ መላኩ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
More Stories
“አንድነታችንን በማጎልበት የህዝብ ጥቅም የሚያስቀድም ፖለቲካ ማራመድ ይጠበቅብናል” ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ
የሕብረ-ብሔራዊ አንድነት መጠናከር መሰረት የሆነው ብዝሃነትን በአግባቡ የማስተናገድ ሂደት ዘርፈ ብዙ ፋይዳ ያለው መሆኑ ተገለፀ
በክረምቱ ወራት ሊከሰቱ የሚችሉ የተለያዩ አደጋዎችን ለመከላከል አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ላይ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ገለጸ