የኬሌ ከተማ ዋና አፈ ጉባኤና የከተማው ከንቲባ ተወካይ ወ/ሮ ሃና ኃይሌ ድጋፍ የተደረገላቸው ተረጂዎች ጀርባ ሌሎች መኖራቸውን በማስታወስ ሁሉም ሰው የመረዳዳት ባህል ማጎልበት እንደሚገባው አስረድተዋል።
የድጋፉን ቁሳቁስ ያሰባሰቡት በኬሌ ከተማ ሴቶች፣ ህፃናትና ወጣቶች ጉዳይ ጽ/ቤት የቀድሞ ኃላፊ ወ/ሮ ርብቃ ታዬ ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ መሆኑን አስታውሰው ድጋፉን ያበረከቱ አካላትና ጊዜያቸውንና ጉልበታቸውን ሰውተው ያገለገሉ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶችን አመስግነዋል።
በኬሌ ከተማ ሴቶች፣ ህፃናትና ወጣቶች ጉዳይ ጽ/ቤት የወጣቶች ማካተትና ንቅናቄ ተሳትፎ ቡድን መሪ አቶ ዳግም ጀምቦ እንደገለጹት፤ የአልባሳትና የትምህርት ቁሳቁስ የተደረገው ለ1መቶ 20 በላይ አረጋውያን፣ ወላጅ ላጡና ለአደራ ልጆች ነው።
ዘጋቢ: ምርጫ መላኩ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
More Stories
ተማሪዎች በወቅቱ ትምህርት ቤት ቀርበዉ እንዲመዘገቡ ወላጆች የሚጠበቅባቸዉን ኃላፊነት እንዲወጡ ጥሪ ቀረበ
የተጀመሩ የልማትና መልካም አስተዳደር ተግባራት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የሀዲያ ዞን ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ተናገሩ
በሆሳዕና ከተማ እየተገነባ ያለውን የመንገድና የኮሪደር ልማት ስራ በታቀደው ጊዜ በጥራትና በፍጥነት ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ