የኬሌ ከተማ ዋና አፈ ጉባኤና የከተማው ከንቲባ ተወካይ ወ/ሮ ሃና ኃይሌ ድጋፍ የተደረገላቸው ተረጂዎች ጀርባ ሌሎች መኖራቸውን በማስታወስ ሁሉም ሰው የመረዳዳት ባህል ማጎልበት እንደሚገባው አስረድተዋል።
የድጋፉን ቁሳቁስ ያሰባሰቡት በኬሌ ከተማ ሴቶች፣ ህፃናትና ወጣቶች ጉዳይ ጽ/ቤት የቀድሞ ኃላፊ ወ/ሮ ርብቃ ታዬ ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ መሆኑን አስታውሰው ድጋፉን ያበረከቱ አካላትና ጊዜያቸውንና ጉልበታቸውን ሰውተው ያገለገሉ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶችን አመስግነዋል።
በኬሌ ከተማ ሴቶች፣ ህፃናትና ወጣቶች ጉዳይ ጽ/ቤት የወጣቶች ማካተትና ንቅናቄ ተሳትፎ ቡድን መሪ አቶ ዳግም ጀምቦ እንደገለጹት፤ የአልባሳትና የትምህርት ቁሳቁስ የተደረገው ለ1መቶ 20 በላይ አረጋውያን፣ ወላጅ ላጡና ለአደራ ልጆች ነው።
ዘጋቢ: ምርጫ መላኩ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በክልሉ ለሚገኙ የዘርፉ ባለሙያዎች ስልጠና መስጠት ጀመረ
የቅድመ በሽታ መከላከል ተግባራትን በአግባቡ በመፈፀም ጤናማ ትውልድ ለመፍጠር በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የሸዋል ዒድ (ቀሊ ፍቼ) ባህላዊ ስርዓት በስልጤ