ድጋፉን የተረከቡት የጎፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ኢንጂነር ዳግማዊ አየለ ቅን ልብ ካላቸው ኢትዮጵያውያን መካከል አንዱ የሆኑት ማስተር አብነት፤ ኢትዮጵያዊነት ምን ማለት እንደሆነ በተግባር ያሳዩ የቁርጥ ቀን ልጃችን ናቸው ብለዋል።
ማስተር አብነት አደጋው ከተከሰተበት ጊዜ ጀምሮ ክስተቱ ከኢትዮጵያ አልፎ በዓለምአቀፍ ደረጃ እንዲታወቅና ተጎጂዎች ሰብዓዊ ድጋፍ እንዲያገኙ በተለያዩ የሚዲያ አውታሮች በማሰራጨት የበኩላቸውን ድርሻ እየተወጡ መቆየታቸውን ተናግረዋል።
ማስተር አብነት ለተጎጂዎች በራሳቸው ከሚያደርጓቸው ድጋፎች በተጨማሪ ኢትዮጵያውያንና በተለያዩ ዓለም ሀገራት የሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያውያን ድጋፍ እንዲያደርጉ በማስተባበር ላሳዩት ኢትዮጵያዊነት በዞኑ አስተዳደርና በተጎጂ ቤተሰቦች ስም ኢንጂነር ዳግማዊ አመስግነዋል።
በዕለቱ የምስጋና ምስክር ወረቀት ከጎፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ኢንጂነር ዳግማዊ አየለ እጅ ለማስተር አብነት ከበደ ተበርክቶላቸዋል።
ማስተር አብነት ድጋፉን ባስረከቡበት ወቅት፥ በደረሰው ድንገተኛ የመሬት መንሸራተት አደጋ በርካታ ዜጎች ሕይወታቸውን ማጣታቸውን ገልጸው፤ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን እንዲሁም ዓለምአቀፉ ማህበረሰብ ድጋፍ እንዲያደርጉ የበኩላቸውን ድርሻ ሲወጡ መቆየታቸውን ተናግረዋል።
በቀጣይ ተጎጂዎች በዘላቂነት እስኪቋቋሙ ድረስ የሚያደርጉትን ሰብዓዊና ቁሳዊ ድጋፍ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ማስተር አብነት ተናግረዋል።
ዘጋቢ: አወል ከድር – ከሳውላ ጣቢያችን

More Stories
በሀሬ ተፋሰስበ በ27 ቀናት ወስጥ 35 ሄክታር መሬት ላይ እርከን ፣ አፈር እቀባና የተለያዩ ዕፅዋት ተከላ መከናወኑ ተገለፀ
አዲሱ የቦንጋ ከተማ መዋቅራዊ ፕላን የኡፋ እና የውሽውሽ ከተሞችን ያካተተ መሆኑን በሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የከተማ ልማት ዲን አቶ ደጉ በቀለ ገለጹ
የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በየዓመቱ ህዳር 29 ቀን እንዲከበር ሲወሰን ዓላማው ብሔር ብሔረሰቦች ባህሎቻቸውን በመለዋወጥ ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በማጠናከር ሃገራዊ መግባባትን እንዲፈጥሩ ማድረግ ነው – የኢፌዴሪ ፌዴሬሽን ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር