የሳውላ ደምባ ጎፋ ወረዳ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ምክትል ሰብሳቢ አቶ መሐመድ ሲረጅ ህዝበ ሙስሊሙ 1ሺ 499ኛውን የመውሊድ በዓልን ሲያከብር የተቸገሩትን ወገኖችን ከማብላትና ከማጠጣት ባለፈ የሀገር ሠላምና አንድነት እንዲጠናከር ዱዓ በማድረግ መሆን እንዳለበት ተናግረዋል።
በአሉ በእስልምና አስተምህሮ ትልቅ ስፍራ የሚሰጣቸውን ነብዩ ሙሀመድ የተወለዱበትን ዕለትና ለሰው ልጆች ያስተማሩትን መልካምና በጎ ስራ ለመዘከር ታስቦ እንደሚከበር ገልጸዋል።
የሳውላ ፈትህ መስጅድ የሞሊድ በዓል አዘጋጅ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ መሐመድ ኢብራሂም በበኩላቸው የነብዩ መሐመድ የመውሊድ በዓል ለአለማት እዝነት እና ሰላም ተደርጎ ወደዚች ምድር የመጡበት ዕለት በመሆኑ የደስታና የመተሳሰብ ቀን መሆኑን ተናግረዋል።
የመውሊድ በዓልን ስናከብር የነብዩ መሐመድን አስተምህሮትን በመከተል ሊሆን እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
ካነጋገርናቸው የበዓሉ ተሳታፊዎች መካከል አቶ መሐመድ አህመድ፣ ወ/ሮ ሶፊያ የሱፍ እና ወ/ሮ ሶፊያ በድሩ ከታላቁ ነብይ መልካም ስብዕናን፣ ለሰው አሳቢነትና ርህራሄ የምናስታውስበት በመሆኑ የእሳቸውን ክብርና ሀቅ በጠበቀ መልኩ ቀኑን ማሳለፋቸውን ተናግረዋል
ህዝበ ሙስሊሙ በዓሉን ሲያከብር የእሳቸውን መልካምነት በመላበስ የተቸገሩትን በመርዳት፣ ሰላም፣ ፍቅርና እዝነትን በተግባር በማሳየት መሆን እንዳለበት ገልጸዋል።
ዘጋቢ፡ አይናለም ሰለሞን- ከሳውላ ጣቢያችን

More Stories
የሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ በስፖርትና ባህል ልማት ዘርፍ የሚገኘውን ተጠቃሚነት ለማሳደግ አበክሮ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
ህግና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን ፍትህ ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት ሥራ አፈፃፀም አደመጠ
ከተማዋን ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ እንደሚሠራ የዲላ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ