በይርጋጨፌ ከተማ የኑሪ መስጂድ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ሳበሀ አለሙ 1 ሺህ 499ኛው የመውሊድ በዓል ሀይማኖታዊ እሴቱን ጠብቆ መከበሩን ገልጸው ለአረጋውያን፣ ለአቅመ ደካሞችና ለጎዳና ተዳዳሪዎች የማዕድ ምገባ ሥነ ስርዓት መከናወኑንም አክለዋል፡፡
በህዝበ ሙስሊሙ መካከል የቆየው አንድነትና ሠላም ተጠናክሮ እየተሠራ መሆኑን የገለጹት አቶ ሳበሀ ለመላው የእምነቱ ተከታዮች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
ከእስልምና እምነት ተከታዮች መካከል አቶ ሰዒድ አሊና ወ/ሮ ሙውባ ደልታታ ህዝቤ ሙስሊ አቅመ ደካሞችን የተቸገሩት በመርዳት በዓሉን እንደሚያከብሩ ተናግረዋል፡፡
ወጣት ጃፈር መሀመድና ጓደኞቹ 1 ሺህ 499ኛው የመውሊድ ምክንያት በማድረግ በበጎ ሥራ ተሰማርተው አባቶችን በማገዝ፣ እርድ በማከናወን በምገባ ሥራ መሳተፋቸውን ገልጸዋል፡፡
ዘጋቢ፡ እምነት ሽፈራው – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
More Stories
“አንድነታችንን በማጎልበት የህዝብ ጥቅም የሚያስቀድም ፖለቲካ ማራመድ ይጠበቅብናል” ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ
የሕብረ-ብሔራዊ አንድነት መጠናከር መሰረት የሆነው ብዝሃነትን በአግባቡ የማስተናገድ ሂደት ዘርፈ ብዙ ፋይዳ ያለው መሆኑ ተገለፀ
በክረምቱ ወራት ሊከሰቱ የሚችሉ የተለያዩ አደጋዎችን ለመከላከል አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ላይ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ገለጸ