በይርጋጨፌ ከተማ የኑሪ መስጂድ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ሳበሀ አለሙ 1 ሺህ 499ኛው የመውሊድ በዓል ሀይማኖታዊ እሴቱን ጠብቆ መከበሩን ገልጸው ለአረጋውያን፣ ለአቅመ ደካሞችና ለጎዳና ተዳዳሪዎች የማዕድ ምገባ ሥነ ስርዓት መከናወኑንም አክለዋል፡፡
በህዝበ ሙስሊሙ መካከል የቆየው አንድነትና ሠላም ተጠናክሮ እየተሠራ መሆኑን የገለጹት አቶ ሳበሀ ለመላው የእምነቱ ተከታዮች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
ከእስልምና እምነት ተከታዮች መካከል አቶ ሰዒድ አሊና ወ/ሮ ሙውባ ደልታታ ህዝቤ ሙስሊ አቅመ ደካሞችን የተቸገሩት በመርዳት በዓሉን እንደሚያከብሩ ተናግረዋል፡፡
ወጣት ጃፈር መሀመድና ጓደኞቹ 1 ሺህ 499ኛው የመውሊድ ምክንያት በማድረግ በበጎ ሥራ ተሰማርተው አባቶችን በማገዝ፣ እርድ በማከናወን በምገባ ሥራ መሳተፋቸውን ገልጸዋል፡፡
ዘጋቢ፡ እምነት ሽፈራው – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
More Stories
በስብዕና ግንባታ ስራ ላይ በማተኮር በስነ-ምግባር የታነፀ ዜጋን ለማፍራት በትኩረት እየሰራ መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ጽህፈት ቤት ገለፀ
ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ለአረጋዉያን ያስገነባዉን የመኖሪያ እና እንክብካቤ ማዕከል ስራ አስጀመረ
የትምህርት ዘርፍ መጠናከር ሀገሪቱ ወደ አዲስ የስልጣኔ ማማ ለመድረስ ለምታደርገው ጉዞ ከፍተኛ ሚና እንዳለው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ውሃ፣ መስኖና ማዕድን ልማት ቢሮ አስታወቀ