በይርጋጨፌ ከተማ የኑሪ መስጂድ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ሳበሀ አለሙ 1 ሺህ 499ኛው የመውሊድ በዓል ሀይማኖታዊ እሴቱን ጠብቆ መከበሩን ገልጸው ለአረጋውያን፣ ለአቅመ ደካሞችና ለጎዳና ተዳዳሪዎች የማዕድ ምገባ ሥነ ስርዓት መከናወኑንም አክለዋል፡፡
በህዝበ ሙስሊሙ መካከል የቆየው አንድነትና ሠላም ተጠናክሮ እየተሠራ መሆኑን የገለጹት አቶ ሳበሀ ለመላው የእምነቱ ተከታዮች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
ከእስልምና እምነት ተከታዮች መካከል አቶ ሰዒድ አሊና ወ/ሮ ሙውባ ደልታታ ህዝቤ ሙስሊ አቅመ ደካሞችን የተቸገሩት በመርዳት በዓሉን እንደሚያከብሩ ተናግረዋል፡፡
ወጣት ጃፈር መሀመድና ጓደኞቹ 1 ሺህ 499ኛው የመውሊድ ምክንያት በማድረግ በበጎ ሥራ ተሰማርተው አባቶችን በማገዝ፣ እርድ በማከናወን በምገባ ሥራ መሳተፋቸውን ገልጸዋል፡፡
ዘጋቢ፡ እምነት ሽፈራው – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
የሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ በስፖርትና ባህል ልማት ዘርፍ የሚገኘውን ተጠቃሚነት ለማሳደግ አበክሮ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
ህግና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን ፍትህ ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት ሥራ አፈፃፀም አደመጠ
ከተማዋን ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ እንደሚሠራ የዲላ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ