በኮንታ ዞን ጪዳ ከተማ የሚኖሩ የእምነቱ ተከታዮች መካከል ካነጋገርናቸው የእስለምና እምነት ተከታዬች መካከል አህመድ አባፊጣ እና መሀመድ አባፊጣ እንደተናገሩት በዓሉ ሲከበር ነብዩ መሀመድ (ሱ.ዓ.ወ) በህይወት ዘመናቸው ያከናወኗቸውን መልካም ተግባራቶችን በማውሳትና የርሳቸውን ታሪክ በማንሳትና በማወደስ ለሌሎች ትምህርት እንዲሆን በደመቀ ሁኔታ እነደሚያከብሩ ተናግረዋል።
አቶ ጅፋር አባፊጣ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጽያ ህዝቦች ክልል የእስልምና ጉዳይ ተቀዳሚ ም/ል ፕረዝደንት እና የኮንታ ዞን የእስልምና ተወካይ ህዝበ ሙስሊሙ 1ሺህ 499ኛው የመውሊድ በዓልን ሲያከብር የተቸገሩ ወገኖችን በማብላትና በማልበስም ጭምር መሆን እንዳለበት ተናግረዋል።
በአሉ በእስልምና አስተምህሮት መሰረት ትልቅ ስፍራ የሚሰጣቸውን ነብዩ ሙሀመድ(ሰ.ዐ.ወ) የተወለዱበትን ዕለት ለማሰብና እርሳቸው ለትውልድ ሁሉ ያስተማሩትን እና ያስተላለፉትን መልካምና በጎ ስራ ለመዘከርና ለማወደስ ታስቦ ዕለቱ እንደሚከበር ገልጸዋል።
ዘጋቢ: ፋሲካ ሙሉጌታ – ከዋካ ጣቢያች

More Stories
የቃል ኪዳን ቤተሰብ ምስረታ ለዘላቂ ሠላም ግንባታ ጉልህ ፋይዳ መኖሩን የሠላም ሚኒስቴር ገለፀ
የሴቶችና ህፃናት ጥቃት ለመከላከል ቅድሚያ ከራስ መጀመር እንደሚገባ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ኤርሲኖ አቡሬ ገለፁ
በተለያዩ የልማት መስኮች ሴቶችን በማሳተፍ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ እየተሰራ መሆኑ ተመላከተ