ሀዋሳ፡ መስከረም 02/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በኮሬ ዞን የኬሌ ከተማ አስተዳደር የአዲስ ዓመት በዓልን ምክንያት በማድረግ ለአቅመ ደካማ ወገኖች፣ ጎዳና ተዳዳሪዎችና ለህግ ታራሚዎች የማዕድ ማጋራት ፕሮግራም አካሄደ፡፡
የኬሌ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ኢንጂነር ዮሐንስ ኃይሉ፣ ማዕድ ማጋራት በህብረተሰቡ ዘንድ የተለመደ መሆኑን በመግለጽ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የኮሬ ልማት ማህበር ሥራ አስኪያጅ አቶ ዳግም ታደሰ በበኩላቸው ማዕድ ማጋራት የአብሮነት መገለጫ መሆኑን አብራርተዋል።
የማዕድ ማጋራት ፕሮግራም የተዘጋጀው 4 መቶ በላይ ለሚሆኑ አቅመ ደካሞች፣ በተለያዩ ምክንያቶች ወላጅ ላጡ ህፃናትና ለህግ ታራሚዎች መሆኑን የተናገሩት የኬሌ ከተማ አስተዳደር ሴቶች፣ ወጣቶችና ህፃናት ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ርብቃ ታየ ናቸው።
የድጋፉ ገንዘብ የተገኘው ከኮሬ ዞን፣ ከከተማው አስተዳደርና አመራሮች ሲሆን የከተማው በጎ አድራጊ ወጣቶች በጉልበታቸው አስተዋጽኦ አድረገዋል ብለዋል ወ/ሮ ርብቃ።
ዘጋቢ: ምርጫ መላኩ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
More Stories
“አንድነታችንን በማጎልበት የህዝብ ጥቅም የሚያስቀድም ፖለቲካ ማራመድ ይጠበቅብናል” ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ
የሕብረ-ብሔራዊ አንድነት መጠናከር መሰረት የሆነው ብዝሃነትን በአግባቡ የማስተናገድ ሂደት ዘርፈ ብዙ ፋይዳ ያለው መሆኑ ተገለፀ
በክረምቱ ወራት ሊከሰቱ የሚችሉ የተለያዩ አደጋዎችን ለመከላከል አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ላይ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ገለጸ