ጳጉሜ 5 የነገ ቀን በሚል መሪ ቃል በጌዴኦ ዞን በዲላ ከተማ ተከብሯል፡፡
የዓመቱ የመጨረሻ ቀን ሆኖ በተከበረው “የነገ” ቀን ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር) ለነገ ኢትዮጵያ ብልጵግና አቅም እንዲሆን በማሰብ ዛሬ ላይ በርካታ የተጀመሩ ሥራዎች መኖራቸውን ተናግረዋል፡፡
የአካባቢ ጥበቃ ሥራና በዩኔስኮ የተመዘገበው የአካባቢው ምህዳር አጠባበቅ ሥርዓት የነገውን ብልጽግና እውን ለማድረግ ታሳቢ ተደርጎ እየተሠራ ነው ብለዋል፡፡
የነገውን ትውልድ ሊጠቅሙ የሚችሉ አሻራ የማሳረፍ ሥራ ከዳር እንዲደርስ ተግቶ መስራት የሚጠይቅ በመሆኑ በቡናና በሌሎች ዘርፎች የተጀመረው ሥራ መጠናከር እንዳለበትም ገልፀዋል፡፡
በልዩ ልዩ መርሀ-ግብሮች እየተከበረ ባለው የነገ ቀን ላይ የተገኙ የተለያዩ የዲላ ክላስተር የቢሮ ኃላፊዎች፣ የዞን ኃላፊዎች፣ የዲላ ከተማ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ ባለሙያዎችና የአካባቢው ነዋሪዎች በከተማው የተሠሩ የልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል፡፡
ዘጋቢ፡ እምነት ሽፈራው – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የፍትህና የጸጥታ ዘርፍ አመራሮችና ባለሙያዎች ሚና የላቀ መሆኑ ተገለጸ
ከአየር ንብረት ተፅዕኖ ጋር እየተስተዋሉ ያሉትን ችግሮች ለመከላከል ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ባለስልጣን አስታወቀ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በክልሉ ለሚገኙ የዘርፉ ባለሙያዎች ስልጠና መስጠት ጀመረ