በሄኖክ አበራ
ተግባቦት||Communication ለሰው ልጅ መሰረታዊ ከሆኑ ክህሎቶች አንዱ ነው።
የተግባቦት ክህሎት የሚጎድለው ሰው ለመኖር ይቸገራል።
መኖር ከራስ, ከሌላ ሰው, ከእንስሳት, ከተፈጥሮ, ከብዙሃን, ከማህበረሰብ ጋር ያለ ተግባቦት የሚታሰብ አይደለም።
መጀመሪያ ግን ከማን ጋር እንግባባ? በኔ እይታ ብዙሃኑም እንደሚጋሩት አስቀድሞ ከራስ ጋር መግባባት ይጠቅማል።
ከተግባቦት( |Communication) አይነቶች አንድኛው Intrapersonal communication ነው።
ህልማችን , በዉስጣችን አሊያም ደግሞ ቃል አዉጥተን ለብቻችን የምናደርገው ንግግር , የምናስበው ሀሳብ , ማሰላሰል ወይንም አርምሞ የ Intrapersonal communication መገለጫዎች ናቸው።
ይህ ተግባቦት ስለራሳችን ያለንን ግንዛቤ እንድናሳድግ , የመወሰን አቅማችን እንዲሻሻል , ጭንቀትና ስጋት እንዲቀንስ እና በራስ መተማመን እንዲጨምር ያስችላል።
ከራሳቸው ጋር የመግባባት ክህሎት ያላቸው ከሌሎች ጋር ለመግባባት አይቸገሩም። ከራስ ጋር መጣላት ከሌላ ጋር ላለመግባባት ምክንያት ይሆናል። እናም መጀመሪያ ከራሳችን ጋር መግባባት ላይ ትኩረት ብናደርግ የተሳካ ተግባቦት ይኖረናል። ከዚያም ከሌሎች ጋር ለመግባባት አንቸገርም።
የ Interpersonal communication ክህሎት ጥቅሙ ብዙ ነው። ይህ ክህሎት መናገርን ማድመጥን እንዲሁም ጠሊቅ አሳቢነትን ያካትታል።
የራስን ፍላጎት በግልጽ ቋንቋ ለማስረዳት ከሌሎችም ጋር ዉጤታማ ግንኙነት ለማድረግ ይረዳል።
ጤናማ የሆነ የግል እና የሙያ ግንኙነት ለመመስረት ያግዛል።
በአጠቃላይ ከራሳችን አሊያም ከሌሎች ጋር የምኖረን ተግባቦት ውጤታማነት በግልም ሆነ በጋራ ህይወት በቤተሰብም ሆነ በስራ አዎንታዊ አስተዋጽኦ ያበረክታል።
እናም በአዲስ ዓመት ከማን ጋር እንግባባ? ጥያቄ
ከሌሎች ለመግባባት ከራስ መግባባት ይቀድማልና የተግባቦት ስርዓታችን አካሄድ ከራስ መጀመር አለበት ብዬ አስባለሁ።

More Stories
በሀሬ ተፋሰስበ በ27 ቀናት ወስጥ 35 ሄክታር መሬት ላይ እርከን ፣ አፈር እቀባና የተለያዩ ዕፅዋት ተከላ መከናወኑ ተገለፀ
አዲሱ የቦንጋ ከተማ መዋቅራዊ ፕላን የኡፋ እና የውሽውሽ ከተሞችን ያካተተ መሆኑን በሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የከተማ ልማት ዲን አቶ ደጉ በቀለ ገለጹ
የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በየዓመቱ ህዳር 29 ቀን እንዲከበር ሲወሰን ዓላማው ብሔር ብሔረሰቦች ባህሎቻቸውን በመለዋወጥ ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በማጠናከር ሃገራዊ መግባባትን እንዲፈጥሩ ማድረግ ነው – የኢፌዴሪ ፌዴሬሽን ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር