“ኅብራችን ለሰላማችን” በሚል መሪ ቃል ነው ጳጉሜን 4 – የኅብር ቀን የተከበረው።
የፕሮግራሙ መክፈቻ የተለያዩ ስፖርታዊ ትርዒቶች፣ በባህላዊና በዘመናዊ ውዝዋዜ በደመቀ ሁኔታ ተከብሯል፡፡
ከልዩ ልዩ ዝግጅት በኋላ በተካሄደው በፓናል ውይይት መድረክ የመክፈቻ መልዕክት ያስተላለፉት የጌዴኦ ዞን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን መምሪያ ኃላፊ ወ/ሮ ዜና ማሞ፣ የህብር ቀን ስናከብር ባለብዙ መልክ የሆነችውን ኢትዮጵያን ለማጽናት የሚከፋፍሉ ትርክቶች ከማጉላት ህብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በሚያጠናክሩ ጉዳዮች ማትኮር መቻል አለብን ብለዋል፡፡
ብዙ ሆነን አንድ፤ አንድ ሆነን ብዙ በመሆን የተገኘውን የሀገራችንን የአብሮነት እሴት በማድመቅ ዘላቂ ሠላም ማስፈንና ሀገረ መንግሥት መገንባት አለብን ብለዋል ወ/ሮ ዜና፡፡
የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ የፖለቲካና ርዕዮተ አለም እና የህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ተስፋጽዮን ዳካ፤ አሮጌውን አመት በብዙ ፈተናዎች ውስጥ ሆነን በጉልህ ስኬቶች በማለፍ ለዛሬው ቀን መድረሳችንን ተናግረዋል፡፡
በአዲሱ አመት የህብረ ብሔራዊ አንድነትን በማጠናከር የሚያጋጥሙ ፈተናዎችን በድል በማሸነፍ ልማትና ሠላም ለማስፈን ሁላችንም በትጋትና በጽናት መስራት ይኖርብናል ብለዋል፡፡
በመርሃግብሩ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ዲላ ክላስተር ቢሮ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች፣ የዞን፣ የዲላ ከተማ፣ የዲላ ዙሪያ ወረዳ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ የፀጥታ አካላት እና ነዋሪዎች ተሳትፈዋል፡፡
ዘጋቢ፡ እምነት ሽፈራው – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
More Stories
የ2018 የኢትዮጵያ የግብርና ናሙና ጥናት መረጃ ሰብሳቢዎች ስልጠና እየተሰጠ ነው
ወረዳው በስፋት እየለማ ያለውን የስንዴ ምርጥ ዘር ለክልሉ ዞኖች ማከፋፈል መጀመሩን አስታወቀ
ህዝበ ሙስሊሙ ከአካባቢ አልፎ በሀገር አቀፍ ደረጃ አንድነትና ሠላም እንዲረጋገጥ እየሠራ እንደሚገኝ የኣሪ ዞን የእስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ገለፀ