በሪፎርም ቀን በዞን ማዕከልና የዲላ ከተማ የመንግሥት ሠራተኞ በጋራ በዲላ ከተማ እያከበሩ ይገኛሉ፡፡
“ሪፎርም ለላቀ አገልግሎት “በሚል መሪህ እየተከበረው ባለው መድረክ የተገኙት የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር) የተለያዩ የሪፎርም ማሻሻያዎችን በመቅረጽና በመተግበር ስልጡን ሲቪል ሰርቪስ ለመፍጠር በትኩረት እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ከኪራይ ሰብሳቢነትና ከሙስና አመለካከት የፀዳ አገልግሎት ለመስጠትም ሪፎርሙ ጉሊህ ሚና አለው ነው ያሉት፡፡
የተሻለ አከባቢ ለመፍጠርና መልካም አስተዳደርን ለማስፈን በሚደረገው ርብርብ ሁሉም የመንግሥት ሠራተኞች በንቃት በመሳተፍ የበኩላቸውን እንዲወጡ ዶክተር ዝናቡ አሳስበዋል፡፡
የዞኑ ትምህርት መምሪያና የዕለቱ መርሃግብር አስተባባሪ አቶ ዘማች ክፍሌ ለህብረተሰቡ ውጤታማ አገልግሎት ከመስጠትና መልካም አስተዳደርን ከማስፈን አንፃር በርካታ ጉድለቶች መኖራቸውን ጠቅሰው የሪፎርም ቀን መከበሩ በዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት የጋራ መግባባት ለመፍጠር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው አመላክተዋል፡፡
ዘጋቢ፦ እምነት ሽፈራው- ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
More Stories
አካል ጉዳተኞች መብቶቻቸውና ጥቅሞቻቸውን ለማስጠበቅ በቅንጅትና በጥምረት መስራት እንደሚገባ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ገለፀ
አካባቢን በመጠበቅና በማጽዳት ምቹና ጽዱ ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት በማገዝ ሁሉም የድርሻውን ልወጣ እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር እንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ አሳሰቡ
ግለሰባዊ ነጠላ ትርክቶችን በጋራ በመታገል በመደመር እሳቤ ችግሮችን መፍታት እንደሚገባ ተገለጸ