በሪፎርም ቀን በዞን ማዕከልና የዲላ ከተማ የመንግሥት ሠራተኞ በጋራ በዲላ ከተማ እያከበሩ ይገኛሉ፡፡
“ሪፎርም ለላቀ አገልግሎት “በሚል መሪህ እየተከበረው ባለው መድረክ የተገኙት የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር) የተለያዩ የሪፎርም ማሻሻያዎችን በመቅረጽና በመተግበር ስልጡን ሲቪል ሰርቪስ ለመፍጠር በትኩረት እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ከኪራይ ሰብሳቢነትና ከሙስና አመለካከት የፀዳ አገልግሎት ለመስጠትም ሪፎርሙ ጉሊህ ሚና አለው ነው ያሉት፡፡
የተሻለ አከባቢ ለመፍጠርና መልካም አስተዳደርን ለማስፈን በሚደረገው ርብርብ ሁሉም የመንግሥት ሠራተኞች በንቃት በመሳተፍ የበኩላቸውን እንዲወጡ ዶክተር ዝናቡ አሳስበዋል፡፡
የዞኑ ትምህርት መምሪያና የዕለቱ መርሃግብር አስተባባሪ አቶ ዘማች ክፍሌ ለህብረተሰቡ ውጤታማ አገልግሎት ከመስጠትና መልካም አስተዳደርን ከማስፈን አንፃር በርካታ ጉድለቶች መኖራቸውን ጠቅሰው የሪፎርም ቀን መከበሩ በዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት የጋራ መግባባት ለመፍጠር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው አመላክተዋል፡፡
ዘጋቢ፦ እምነት ሽፈራው- ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
በጎፋ ዞን ዛላ ወረዳ ከ13 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባ ንጹህ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ግንባታ ተጠናቆ ተመረቀ
በሀድያ ዞን ሌሞ ወረዳ ከ5 ሺህ 9 መቶ በላይ ተማሪዎች ክልላዊና ሀገር አቀፍ ብሔራዊ ፈተና ለመውሰድ ዝግጅት እያደረጉ መሆናቸው ተገለፀ
”ከተረጅነት ወደ ምርታማነት” በሚል መሪ ሃሳብ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በሀዋሳ ከተማ የውይይት መድረክ በመካሄድ ላይ ነው