ቢሮው የሪፎርም ቀንን አስመልክቶ ከሠራተኞች ጋር ውይይት አካህዷል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኢንዱስቲሪ ልማት ቢሮ ሀላፊ ዶ/ር እንዳልካቸው ጌታቸው እንዳሉት መንግሥት ሀገራዊ ልማት ለማፋጠን ከያዛቸው ዋና ዋና ግቦች አንዱ የሆነውን የአምራች የኢንዱስቲሪ ልማት ዘርፍ በማጠናከር በባለፈው ዓመት የተጀመሩ አመርቂ ውጤቶችን በአዲሱ ዓመት በአዲስ ተስፋ ሰን ቀን በትጋት መሥራት ይጠበቅብናል ነው ያሉት።
በሪፎርም ቀኑ ሁሉም የቢሮው ሠራተኞች እና አመራሮች ተገኝተው አገልግሎት የሠጡ ሲሆን ለአዲስ ዓመት የመልካም ምኞት ስጦታም ተለዋውጠዋል።
ይህም የቢሮ ሠራተኛው እርስ በርስ ይበልጥ በመቀራረብ ለላቀ ውጤት ለመትጋት ተነሣሽነትን እንደምፈጥር የገለጹት ደግሞ የቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ መንግሥቱ ተክለ ናቸው።
የቢሮ ሠራተኞች የሪፎርሙን ቀን አስመልክተው መደበኛ ሥራቸውን በማከናወን ላይ መሆናቸው ተመልክቷል።
ዘጋቢ ፡ ወ/ገብርኤል ላቀው- ከአርባ ምንጭ ጣቢያችን

More Stories
የእምነት ተቋማት ለአገረ መንግስት ግንባታ ቁልፍ ሚና ያላቸው በመሆኑ ለሀገር ብልጽግና ኃይል አድርጎ መጠቀም እንደሚገባ ተመላከተ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የኢትዮጵያ ብልፅግና እንዲረጋገጥ አዎንታዊ አስተዋጽኦ ማበርከቷ ተገለጸ
ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በተገኙበት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አባቶችና ምዕመናን ክልል አቀፍ የምክክር መድረክ እየተካሄደ ነው