ቢሮው የሪፎርም ቀንን አስመልክቶ ከሠራተኞች ጋር ውይይት አካህዷል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኢንዱስቲሪ ልማት ቢሮ ሀላፊ ዶ/ር እንዳልካቸው ጌታቸው እንዳሉት መንግሥት ሀገራዊ ልማት ለማፋጠን ከያዛቸው ዋና ዋና ግቦች አንዱ የሆነውን የአምራች የኢንዱስቲሪ ልማት ዘርፍ በማጠናከር በባለፈው ዓመት የተጀመሩ አመርቂ ውጤቶችን በአዲሱ ዓመት በአዲስ ተስፋ ሰን ቀን በትጋት መሥራት ይጠበቅብናል ነው ያሉት።
በሪፎርም ቀኑ ሁሉም የቢሮው ሠራተኞች እና አመራሮች ተገኝተው አገልግሎት የሠጡ ሲሆን ለአዲስ ዓመት የመልካም ምኞት ስጦታም ተለዋውጠዋል።
ይህም የቢሮ ሠራተኛው እርስ በርስ ይበልጥ በመቀራረብ ለላቀ ውጤት ለመትጋት ተነሣሽነትን እንደምፈጥር የገለጹት ደግሞ የቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ መንግሥቱ ተክለ ናቸው።
የቢሮ ሠራተኞች የሪፎርሙን ቀን አስመልክተው መደበኛ ሥራቸውን በማከናወን ላይ መሆናቸው ተመልክቷል።
ዘጋቢ ፡ ወ/ገብርኤል ላቀው- ከአርባ ምንጭ ጣቢያችን

More Stories
በጎፋ ዞን ዛላ ወረዳ ከ13 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባ ንጹህ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ግንባታ ተጠናቆ ተመረቀ
በሀድያ ዞን ሌሞ ወረዳ ከ5 ሺህ 9 መቶ በላይ ተማሪዎች ክልላዊና ሀገር አቀፍ ብሔራዊ ፈተና ለመውሰድ ዝግጅት እያደረጉ መሆናቸው ተገለፀ
”ከተረጅነት ወደ ምርታማነት” በሚል መሪ ሃሳብ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በሀዋሳ ከተማ የውይይት መድረክ በመካሄድ ላይ ነው